
Press release: UK: Minister for Africa expresses concern over Ethiopian elections June 23, 2015
Posted by OromianEconomist in Sham elections.Tags: 2015 Sham Elections: Marred by rampant electoral fraud, Africa, Hadiyyaa Nation, malpractice and violence by the ruling TPLF to stay on and maintain the 24 years tyrannic rules, Sham elections
add a comment
Mootummaan Biyya Inglizii flannoo Itopiyaatti ta’e ilaalchisee yaaddoo akka qabu ibse.
The UK: Minister for Africa expresses concern over elections in Ethiopia

Post sham elections and the scene of Fascist TPLF Ethiopia’s murder crimes: Berhanu Rebo, Hadiya National and member of Medrek foundation committee murdered June 22, 2015
Posted by OromianEconomist in Sham elections.Tags: Africa, Berhanu Rebo, Ethiopia's sham elections, Hadiyyaa Nation, Medrek, sham, The Tyranny of Ethiopia
add a comment
Mr. Berhanu Rebo, Hadiya National and member of Medrek foundation committee was murdered by Fascist TPLF Ethiopia’s killing squads on 18th June 2015. His body was damped near river bank. Mr. Berhanu Rebo was a resident of Diinaa Tooroo in Sooroo district, Hadiya Zone (Southern State). Mr. Rebo was a husband and father of five.
Jiraataan Biyya Hadiyyaa, konyaa Sooroo, ganda Diinaa Tooroo fi miseena kommiitee bu’uraa partii Madrak kan ta’an lammiin saba Hadiyyaa Obbo Biraanuu Reeboo ergamtoota wayyaaneen Kamisa, Waxabajji 18 Bara 2015 qeyee isaaniitti admfamanii ajjeefamanii laga qaraqara irratti gatamuuni isaan beekame.
Obbo biraanuu Reeboo umurii waggaa 40 yoo ta’ni, abbaa manaa fi abbaa ijoollee shaniiti.
ዜና መድረክ:- በሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ ዳና ቶራ ቀበሌ የኢማዴ-ደህአፓ/መድረክ መሠረታዊ ኮሚቴ አባል አቶ ብርሃኑ ረቦ ተገደሉ
(ዜና መድረክ) – በሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ ዳና ቶራ ቀበሌ የኢማዴ-ደህአፓ/መድረክ መሠረታዊ ኮሚቴ አባል አቶ ብርሃኑ ረቦ ተገደሉ፡፡
በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ በዳና ቶራ ቀበሌ ነዋሪና የኢማዴ-ደህአፓ/መድረክ መሠረታዊ ኮሚቴ አባል የነበሩትና በ2007 ሀገር አቀፍ ምርጫ በቅስቀሳ ሥራ ላይ ተሰማርተው ከፍተኛ አስተዋጾ ሲያበረክቱ የቆዩት አቶ ብርሃኑ ረቦ ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ በመኖሪያ መንደራቸው በተፈጸመባቸው ድብደባ ከተገደሉ በኋላ ወንዝ ውስጥ ተጥለው ተገኝተዋል፡፡ በዕለቱ ይኼው የመድረክ አባሉ ከመገደላቸው በፊት ብርሃኑ ደቦጭና ታዲዮስ ጡምሶ የሚባሉ ፖሊሶች ሟቹንና ሌሎች በቀበሌው የሚኖሩ የመድረክ አባላትን ለመደብደብ ሲያሳድዱ ሟቹ ከአከባቢው ሸሽተው የሄዱ ሲሆን ሌሎቹን አባላት አግኝተው መደብደባቸውና እርሳቸውን ሲፈልጉ ካመሹ በኋላ ማታ ወደቤታቸው ሲመለሱ ጠብቀው ግዲያውን ፈጽመው ወደ ወንዝ ወስደው እንደጣሉ ከአከባቢው ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሎአል፡፡ ከግዲያው ቀደም ባሉት ቀናትም እነዚሁ ፖሊሶች በሟች አቶ ብርሃኑና ሌሎች የመድረክ አባላት ላይ ግዲያ እንደሚፈጽሙና ከአከባቢው እንደሚያጠፉዋቸው ሲዝቱ መቆየታቸውም ታውቋል፡፡
አቶ ብርሃኑ ረቦ የ40 ዓመት ጎልማሳ ሲሆኑ ባለትዳርና የአምስት ልጆች አባት ነበሩ፡፡ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ እንዳልተፈጸመም ለማወቅ ተችሎአል፡፡
በ2007 በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማሸነፉ የሚወራለት የኢህአዴግ ካድሬዎች በአሁኑ ወቅት በምርጫው ቅስቀሳ ንቁ ተሳትፎ ያደረጉ የመድረክ አባላትን በየአከባቢው የማዋከብ፣ የማሰር፣ በገንዘብ የመቅጣት፣ የመደብደብና የመግደል ተግባራትን በማከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን ከምርጫው ዕለት ጀምሮ ከተገደሉት የመድረክ አባላት አቶ ብርሃኑ ረቦ 4ኛው ሟች ናቸው፡፡ ቀደም ስል በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳ ቀኝ ወረዳ አቶ ጊዲሳ ጨመዳ፣ በምዕራበ አርሲ ዞን ቆራ ወረዳ አቶ ገቢ ጥቤ እና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ምዕራብ ትግራ ዞን በማይካድራ ከተማ አቶ ታደሰ አብርሃ የሚባሉ የመድረክ አባላት ከምርጫው ዕለት ጀምሮ መገደላቸው ይታወሳል፡፡ በምርጫው ወቅት መድረክ ጠንካራ እንቅስቃሴ ባደረገባቸው በደቡብ ብ/ብ/ሕ፣ በኦሮሚያና በትግራይ ክልሎች ከምርጫው ወዲህ ብቻ ቤታቸው የተቃጠለባቸው፣ የፈረሰባቸው፣ በጥይት የቆሰሉ፣ በድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውና በእስር በመሰቃየት ላይ የሚገኙት የመድረክ አባላት ቁጥር በብዙ መቶዎች የሚቆጠር ነው፡፡