jump to navigation

Oromia & Ethiopia: Flannoo kijibaa Wayyaanee Caamsaa Darbee Ilaalishisee Ibsa OFC/Medrek: OFC/Medrek’s Statement Regarding Ethiopia’s May 2015 Sham Election June 27, 2015

Posted by OromianEconomist in OFC, Sham elections.
Tags: , , , , ,
add a comment

???????????OFC MEDREK’S Election Symbol (Five Fingers with the Open Palm'High Five Goes Viral

Deja vu in 2015 Ethiopian Elections

በ2007 በኢትዮጵያ የተካሄደውን ምርጫ በሚመለከት ከመድረክ የተሰጠ መግለጫ:- ሕገ-መንግሥታዊና ሕጋዊ የምርጫ ሥርዓት በተጣሰበት ሂደት የተከናወነው ሕገ ወጥ የምርጫ ድራማ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም!

ከመድረክ የተሰጠ መግለጫ …

ሕገ-መንግሥታዊና ሕጋዊ የምርጫ ሥርዓት በተጣሰበት ሂደት የተከናወነው ሕገ ወጥ የምርጫ ድራማ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም!

በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እውን ሆኖ በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ አማካይነት የሕዝባችን የሥልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጥበት ሁኔታ በሕገ-መንግስቱ እውቅና ተሰጥቶት በይፋ ተደንግጎአል፡፡ ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ሕገመንግሥቱንና የምርጫ ሕጎችን የጣሰ የምርጫ ድራማ በየ5 ዓመቱ በመቶ ሚሊዮኖች የሀገር ገንዘብ እያባከነ ያካሂዳል፡፡ ኢህአዴግ ይህንን የምርጫ ድራማ የሚያከሂደው፣ ወቅቱን የጠበቀ ምርጫ ማካሄድ በዓለም አቀፍ ለጋሽ ዴሞክራሲያዊ ሀገሮች ዘንድ እውቅና የስገኝልኛል በሚል ተስፋ ነው፡፡ ተጨባጩ እውነታ የሚያሳየው ግን ኢህአዴግ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው 24 ዓመታት ራሱ ያጸደቃቸውን ሕጋዊና ሕገመንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በመርገጥ የራሱን አምባገነናዊ ገዥነት ለማስቀጠል እንዲያስችለው የሕዝብ ድምፅ መንጠቂያና ማፈኛ ሕገወጥ የምርጫ ስትራቴጂዎችን እያወጣና ሥራ ላይ እያዋለ መሆኑን ነው፡፡ የሕዝባችንን ድምፅ መቀማቱንና ማፈኑን በየምርጫ ዙሮቹ እያባባሰ መሄዱን ቀጥሎበት አሁን ለደረስንበት የ100 ፐርሰንት ቅሚያም ደርሶአል፡፡ በተለይም በ2007 ዓም በተካሄደው የ5ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ሕጋዊና ሕገመንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በማንአለብኝነት በመጣስ በአጋርነት የፈረጃቸውን ፓርቲዎች አስከትሎና ሕዝቡንና ሐቀኛ ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በኃይል አፍኖ ምርጫውን በሕገወጥ መንገድ መቶ በመቶ ለመቆጣጠርና ጠቅልሎ ለመውሰድ የፈጸማቸው አስነዋሪ ተግባራት ከአንድ በመንግሥት ኃላፊነት ላይ ከሚገኝ ፓርቲ የማይጠበቁ ናቸው፡፡ አገዛዙ በዚሁ ምርጫ ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ ከፈጸማቸው ሕገወጥ ተግባራት ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

1ኛ፡- የኢህአዴግ ካድሬዎች ከምርጫ ቦርድ በሚደረግላቸው ትብብር ብዛት ያላቸው የመራጮች ምዝገባ ካርደ እየተሰጣቸው አህአዴግን ይመርጣሉ ለሚሏቸው ቤት ለቤት በመዞር ለአንድ ሰው ከአስር ካርዶች በላይ ከተለያዩ ማስፈራሪያዎችና መደለያዎች ጋር ጭምር የምርጫው ዕለት ድረስ በማደል አንድ ሰው አንድ ድምጽ የሚለውን ሕግ በመጣስ ወንጀል ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡ ተቃዋሚዎችን ይመርጣሉ ብለው የጠረጠሩዋቸውን በርካታ ዜጎችንም የምርጫ ምዝገባው ጊዜ ከማለቁ በፊት በምርጫ አስፈጻሚዎች #መዝገቡ ሞልቷል$ ወይም #ካርዱ አልቋል$ እየተባለ ሳይመዘገቡ እንዲቀሩ ተደርጓል፡፡ እንደዚሁም መድረክ በመረጃ የደረሰባቸውን ለሰው የታደሉ ትርፍ የመራጭ ካርዶችን ከመራጮች ምዝገባ ላይ ለማመሳከር ባደረገው ጥረት ካርዶቹ ተመዝግበው ያለመገኘታቸውን ማረጋገጡ፣ በመራጮች ምዝገባ ሂደት ከፍተኛ ወንጀል እንደተፈጸመ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አዋጅ 532/1999፣አንቀጽ 65 3ለ ላይ የሰፈረውን #እያንዳንዱ መራጭ በመራጮች መዝገብ ላይ ስሙ ሰፍሮ መገኘት አለበት$ የሚለውን ድንጋጌ መጣሱም ምርጫውን ሕገወጥ የሚያደርግ ነው፡፡

2ኛ፡- በየምርጫ ጣቢያዎቹ የሕዝብ ታዛቢዎች ተብለው የተሰየሙት ሰዎችም የምርጫ ደንብ በሚያዘው መሠረት፣ በምርጫ የሚወዳደሩ ፓርቲዎች በደብዳቤ ተገልጾላቸው ተወካዮቻቸው በተገኙበት መመረጥ ሲገባቸው ያለተቃዋሚ ፓርቲዎች ተሳትፎ በአህአዴግ ደጋፊነታቸው የተመለመሉ መሆኑ ምርጫው ነፃና ታአማኒ እንዳይሆን ከመነሻው የተወጠነ ሕገወጥ አካሄድ ነበር፡፡

3ኛ፡- ገዥው ፓርቲ መንግሥታዊ ሥልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም በየክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር ሕግ የተፈቀደውን የቅስቀሳ ጊዜ ፈቃድ ለመድረክ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ከልክሎ የኢህአዴግ አባላት የሆኑ ከፌዴራል እሰከ ወረዳ ደረጃ ያሉት እጅግ በርካታ የመንግሥት ሠራተኞች ዕጩ ተወዳዳሪ ያልሆኑት ጭምር ከሙሉ ክፍያ ጋር ከመደበኛ ሥራቸው ነፃ ሆነው በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት በየተወለዱበት ወረዳዎችና ቀበሌዎች ተሠማርተዋል፡፡ ለምርጫ የተመዘገበውን ሕዝብም ቤት ለቤት እየዞሩ በማስፈራራትና በመደልል የንብ ምልክት ብቻ እንዲመርጡና መምረጣቸውንም ለኢህአዴግ ተወካዮች በግልጽ እያሳዩ ኮሮጆ ውስጥ እንዲጥሉ፣ ይህንን ካላደረጉ ግን ተቃዋሚዎችን እንደመረጡ እንደሚቆጠርና ተለይተውም እንደሚታወቁ በማስጠንቀቅና በማስፈራራት ላይ ተሰማርተው ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ ሕገወጥ ሥራ የተሰማሩት የኢህአዴግ አባላት የሆኑት የመንግሥት ሠራተኞች በብዙ አከባቢዎች የመንግሥት ተሸከርካሪዎችን ለምርጫ ቅስቀሳ በማንአለብኝነት ሲገለገሉበት ቆይተዋል፡፡

4ኛ፡- በምርጫው ሂደት በብዙ ምርጫ ክልሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የመድረክ ዕጩዎችና ቀስቃሾች ሲደበደቡና ከባድ ጉዳት ሲደርስባቸው፣ ሲታሰሩና ለቅስቀሳ የሚጠቀሙባቸውን መሳረያዎች በገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ሲነጠቁና ሲቀሙ ቆይተዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በዳራሞሎ ወረዳ 26፣ በዛለ ወረዳ 19፣ በካምባ ወረዳ 4፣በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ 2፣ በኦሮሚያ ክልል በባሌ ዞን ዶሎ መና ወረዳ 40፣ በቦረና ዞን ቡሌ ሆራ ወረዳ 40፣ በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦና ጀልዱ ወረዳዎች 27፣ በትግራይ ክክል በመቀሌ ከተማ 17 ፣ እስከአሁን በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን በመቶዎች የሚቆጠሩት በዋስ ተፈትው ጉዳያቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡

5ኛ፡- የዜጎችን ነፃና ምስጢራዊ የድምፅ አሰጣጥ መርሕ በመጣስ አንድ አባል 11 መራጮችን መልምሎ እንዲከታተልና ሕዝቡ በ1ለ5 ተጠርንፎ እስከ ምርጫ ጣቢያዎች ድረስ ተያይዞ በመሄድ ድምፅ እንዲሰጥ በገዥው ፓርቲ በተቀየሰው ስተራቴጂ ምርጫው እንዲካሄድ ተደርጓል፡፡ በአከባቢው በሌሉና በማይታወቁ ሰዎች ስምም የተመዘገቡ ካርዶችን በመጠቀም ምርጫው እንዲካሄድ አድርገዋል፡፡ ለምሳሌም በደቡብ ክልል በቀድዳ ጋሜላ ወረዳ ይህ ተፈጽሟል፡፡

6ኛ፡- በምርጫው ዕለት በአብዘኛው ምርጫ ጣቢያዎች የመድረክ ተወካዮች እንዳይገኙ በማባረር፣ በመደብደብና በማሰር ምርጫውን ታዛቢዎቻችን በሌሉበትና የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሆኑት የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ አመራር አባላት የምርጫ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠሩበትና አዋጅ ቁጥር 532/1999 አንቀጽ 47 ንዑስ አንቀጽ 3 በመተላለፍ ልዩ ኃይል ፣የፌዴራል ፖሊስና ታጣቂዎችን በሕዝቡ መካከል በብዛት በማሰማራት በህዝቡ ላይ የሥነ ልቦና ሽብር በፈጠሩበት ሁኔታ ምርጫው ሊካሄድ ችሎአል፡፡ ብዙ የምርጫ ጣቢያዎችንም በርካታ ታጣቂዎች ልዩ ትጥቅ አንግበው እንዲቆጣጠሩት ተደርጓል፡፡ ከበርካታ ምርጫ ጣቢያዎችም በየጣቢያዎቹ ተገኝተው የነበሩት ወኪሎቻችን እየተፈጸሙ ያዩትን የምርጫ ሕግ ጥሰቶች ለማሳረም ሲሞክሩ ተደብድበው ተባረዋል፡፡

7ኛ፡- በበርካታ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ሰነዶች፣ የድምፅ መስጫ ወረቀቶች የምርጫ ጣቢያ የኮድ ማሕተሞችና የኮሮጆ ቁልፎች በሥርዓት ባልተያዙበትና ኮሮጆዎቹ ቀድመው ሞልተው ባደሩበት እንደዚሁም አዲስ የመራጭ ካርድም በአዲስ መልክ ሲታደል በነበረበትና የንብ ምልክት የተደረገባቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ከውጭ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየገቡ ጥቅም ላይ ሲውሉ በነበረበት ሁኔታ የድምፅ አሰጣጡ ተከናውኖአል፡፡

8ኛ፡- ለመድረክ ድምፅ የተሰጠባቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች በብዛት ሽንት ቤት የተጣሉበትና የተቃጠሉበት ሁኔታ በብዙ አከባቢዎች ተከስቶአል፡፡ ለዚሁም ማስረጃ የሚሆኑ በርካታ ከሽንት ቤት የተሰበሰቡ ድምጾች ለአብነት በእጃችን ይገኛሉ፡፡

9ኛ፡- የመራጭ ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ 2/2000፣ አንቀጽ 13/7 # በአንድ ድምፅ መስጫ ጣቢያ ከ1000 በላይ ድምፅ አይሰጥም$ የሚለውን ድንጋጌ በመተላለፍ የኢህአዴግ ተወዳዳሪዎች ከ1000 በላይ ድምጽ እንዳገኙ ተደርጎ ይፋ መደረጉና ይህ እየታወቀ በምርጫ ቦርድም የእርምት እርምጃ አልተወሰደም፡፡

10ኛ፡- በቅድመ ምርጫም ሆነ በምርጫው ዕለት የተከሰቱ የሕግ ጥሰቶችና የኃይል እርምጃዎችን በሚመለከት መድረክ ከምርጫ ጣቢያዎች አንስቶ እስከ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ድረስ ላሉት አካላት ያቀረባቸው ቅሬታዎችና አቤቱታዎች ተገቢው መፍትሔ ሳይሰጣቸው ቀርቶ ችግሩ እየተባባሰ ገዥው ፓርቲ በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት በመመራት የታጠቀ ኃይል በሰላማዊ ሕዝብ ላይ በማዝመት ጭምር ያከናወነው ምርጫ ሊሆን ችሎአል፡፡

11ኛ፡- በምርጫው ዕለት በኦሮሚያ ክልል በምራብ ሸዋ ዞን ሚዳ ቀኝ ወረዳ በአቶ ጊዲሳ ጨመዳ እና በምዕራብ አርሲ ዞን በቆራ ወረዳ በአቶ ገቢ ጥሴቦ ላይ ግድያዎች የተፈጸሙ ሲሆን፣ ከምርጫው በኋላም በምራብ ትግራይ ዞን በማይካድራ ከተማ በአቶ ታደሰ አብርሃና በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል በሀዲያ ዞን በሶሮ ወረዳ በአቶ ብርሃኑ ኤረቦ በሚባሉ በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳትፎ ባደረጉት የመድረክ ሰላማዊ ታጋዮች ላይ አሰቃቂ ግዲያዎች ተፈጽመዋል፡፡ በጋሞጎፋ ዞን በአርባ ምንጭ ምርጫ ክልልም በምርጫው እንቅስቃሴ ጠንካራ ተሳትፎ ባደረገውና በላካ ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ የመድረክ ወኪል/ታዛቢ በነበሩት በአቶ ዳንኤል ጉዴ ላይ በተደረገው የመግደል ሙከራ ከቤተሰባቸው ጋር እቤት ውስጥ ተኝተው እያሉ ቤታቸውን ከውጭ በገመድ አስረው በእሳት በማቃጠል ከነቤተሰባቸው ለመጨረስ ሙከራ የተደረገ ሲሆን የመድረክ አባሉና ቤተሰቡ በጎረቤት እርዳታ ሕይወታቸው ሲተርፍ ቤት ንብረታቸው በሙሉ ተቃጥሎ በአሰቃቂ ሁኔታ ሜዳ ላይ ቀርተው ይገኛሉ፡፡ የሰላም ታጋዩ በአሁኑ ወቅት ከቀበሌአቸው በኢህአዴግ ካድሬዎች የተባረሩ ሲሆን ከአቅመደካማና ቤቱ ከመቃጠሉ በፊት በካድሬዎቹ ክፉኛ ከተደበደቡት አሮጊት እናታቸው ጋር ወደ ቀበሌአቸውም እንዳይመጡ በካድሬዎች ተከልክለው እየተንከራተቱ ይገኛሉ፡፡

12ኛ፡- ከዚህ በላይ በአጭሩ ለመግለጽ በተሞከረበት ሁኔታ በምርጫው የሕዝቡን ድምፅ ጠቅልለው የወሰዱት የኢህአዴግ ካድሬዎች ይህ አስነዋሪ ተግባራቸው አልበቃ ብሎ ከምርጫው ማግስት ጀምረው በብዙ አከባቢዎች #ለመድረክ በታዛቢነት አገልግላችኋል፣ሕዝቡ መድረክን እንዲመርጥ ቅስቀሳ አድርጋችኋል፣ መድረክን መርጣችኋል$ ወዘተ ባሉዋቸው በርካታ ዜጎች ላይ የበቀል እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚሁም መሠረት በተለያዩ አከባቢዎች በርካታ አባሎቻችንን በማሰር፣ በመደብደብ፣ ቤታቸውን በማፍረስና በሐሰት ወንጅሎ በማስቀጣት፣ ከሥራቸውና ከትምህርት ገበታቸው በማባረር፣ የሥልጠና ዕድል በመንፈግና በመንግሥት ሥራ እንዳይቀጠሩም በመከልከል እንደዚሁም በገጠር በግብርና ሥራ ላይ የተሰማሩ አባሎቻችን የሰፍትኔት ዕርዳታና ሌሎች መንግሥታዊ እርዳታዎችንና አገልግሎቶችን እንዳያገኙ በማድረግ ወዘተ የዜግነት መብታቸውን ነፍገው እያሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቻችንንም በግድ ዝጉ በማለት እያስፈራሩ በማዘጋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌም በምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ሮቢ ወረዳ በ16/10/07 በወረዳው አስተዳዳሪና በወረዳው ፖሊስ አዛዥ በተሰጠ ትዕዛዝ የኦፌኮ/መድረክ ቅ/ጽ/ቤት ተዘግቷል፡፡

ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትና በገዥው ፓርቲ የተፈጸሙት ተግባራት በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 54 ንዑስ አንቀጽ 1 #የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምፅ በምስጢር በሚሰጥበት ሥርዓት በየአምስት አመቱ በሕዝብ ይመረጣሉ&$ ተብሎ የተደነገገውን የጣሰ ነው፡፡ እንደዚሁም የየክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫን በሚመለከትም በየክልላዊ መንግሥታቱ ሕገመንግሥታት በተመሳሳይ የተደነገጉትን፣ በተሻሻለው የምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 አንቀፅ 26 በሰፈሩት የምርጫ መርሖዎችም #ማንኛውም ምርጫ ሁሉአቀፍ፣ ቀጥተኛ፣በምስጢር ድምፅ አሰጣጥ መራጩ ፈቃዱን በነፃነት የሚገለጽበት እና ያለምንም ልዩነት በእኩል ሕዝባዊ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ ይሆናል& የመምረጥ መመረጥ መብቱ በሕግ ያልተገደበ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት አለው& እያንዳንዱ መራጭ የሚሰጠው ድምፅ እኩል ነው& ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ለመምረጥም ሆነ ለመመረጥ አይገደድም&$ ተብሎ የተደነገገውንም የጣሰ ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራችን የምርጫ ሥነምግባር ሕግ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 1 ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀምን አስመልክቶ #ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ፡- ያለውን የሥልጣን ኃላፊነትና የተለየ ዕድል ወይም ተፅዕኖ የማሳደር ችሎታ ለፖለቲካ ፍላጎቱ ለመጠቀም መደለያ ማቅረብን፣ ቅጣትንና ማንኛውንም የማስፈራሪያ መንገድ መጠቀምና የፈዴራል መንግሥትን፣ የክልል መንግሥታትን፣ የከተማ ማዘጋጃ ቤትን ወይም ሌላ የሕዝብ ሀብትን በምርጫ ሕጉ ከተፈቀደው አኳኋን ውጭ ለምርጫ ቅስቀሳ ዓላማ መጠቀም የለበትም&$የሚለውንም ድንጋጌ ያላከበረ ነው፡፡ የመንግሥት ሠራተኞችና ንብረት በሚመለከትም የመንግሥት ሠራተኛና ኃላፊ ሆኖ በራሱ የግል ጊዜ ካልሆነ በስተቀር በመንግሥት የሥራ ሰዓትና ኃላፊነት ተቋሙን በመጠቀም እጩዎችን ያስተዋወቀ ወይም ሌሎች እጩዎች ራሳቸውን በሕጋዊ መንገድ ለማስተዋወቅ ያላቸውን እድል ያደናቀፈ፣ በመንግሥት ንብረት ለምርጫ ቅስቀሳ የተጠቀመ፣ እንደሆነ የሥነምግባር ጥሰት እንደፈጸመ ይቆጠራል& ተብሎ በአንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 7 እና 8 የተደነገገውን በመጣስ የተፈጸሙ ሕገወጥ ተግባራት ናቸው፡፡

በአጠቃላይም በ2007 ዓ ም በሀገራችን ተካሄደ የተባለው ምርጫ በሕግና ሥርዓት ያልተመራና በሕገ-መንግሥቱና በምርጫ ሕጎች የተደነገጉትን የነፃ፣ፍትሐዊና ታአማኒነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መርሖዎች በኃይል በተጣሱበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ መድረክ የምርጫውን ሂደትም ሆነ ውጤት የማይቀበለው መሆኑን እየገለጸ፣ ለዚህ አሁን ሀገራችን ለገባችበት አስቸጋሪ ሁኔታ መፍትሔ ለማስገኘት የሚከተሉት እርምጃዎች እንዲወሰዱ በጥብቅ ይጠይቃል፡፡

1ኛ፡– በ2007 ዓ ም የተካሄደው 5ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ሂደትና ክንዋኔ በአጠቃላይ የሀገሪቱን ሕገመንግሥትና የምርጫ ሕጎች በጣሰ ሁኔታ የተከናወነ ስለሆነ፣ ይህንን ግዙፍ የሕግ ጥሰት አንድ ወገንተኛ ያልሆነ አካል ተቋቁሞ እንዲያጣራው፣

2ኛ፡- ከዚህ በላይ በተጠቀሱት አራት አባሎቻችን ላይ ግዲያ የፈጸሙ ወንጀለኞች ተገቢው ክትትል ተደርጎ ለሕግ እንዲቀርቡና ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው፣

3ኛ፡- ከምርጫው ቅስቀሳ ወቅት ጀምሮ በየምርጫ ክልሎቹ የታሰሩት አባሎቻችን ካለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱና የድብደባና የማሰቃየት ተግባራትን የፈጸሙባቸው የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣

4ኛ፡- ከምርጫው እንቅስቃሴ ወዲህ ቤታቸው የተቃጠለባቸው፣ የፈረሰባቸውና ንብረታቸው የተዘረፈባቸው አባሎቻችን ሀብትና ንብረት በአስቸኳይ እንዲመለስላቸውና እንዲከፈላቸው፣ በንብረታቸው ላይ ጉዳት ያደረሱ ካድሬዎችና የጸጥታ ኃይሎች አባላትም በሕግ እንዲጠየቁ፣

5ኛ፡- በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ካድሬዎች በማንአለብኝነት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየፈጸሙ የሚገኙት የማሸበር ተግባራት ማለትም በሰላማዊ ታጋዮቻችን ላይ በቀጣይነት እየተፈጸሙ ያሉት ግዲያዎች፣ ማስፈራራት፣ ወከባዎች፣ ዛቻዎችና የመሥራትና የመማር እንዲሁም እርዳታና አገልግሎት የማግኘት መብት በመንፈግ የሚፈጸሙ ሕገወጥ ተግባራት በአስቸኳይ እንዲቆሙ እንዲደረግና በዚህ አፍራሽና ፀረ ሰላም ተግባራቸው ምክንያት የሀገራችንና የሕዝባችን ሰላምና ደህንነት እንዳይናጋ ወቅታዊ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ፣

6ኛ፡- በ2007 ዓ ም በሀገራችን የተካሄደው ምርጫ ከሀገራችን ሕገ-መንግሥትና የምርጫ ሕጎች ውጭ መንግሥታዊ ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም ሕዝብን በማስፈራራት፣ በኃይልና በአፈና ገለልተኛ ታዛቢዎች በሌሉበት ገዥው ፓርቲ ራሱ ተወዳዳሪ፣ ዳኛና ታዛቢ ሆኖ ያካሄደውና በምንም መልኩ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ያልሆነና ታአማኒነት የሌለው ሕገወጥ ምርጫ ስለሆነ፣ገዥው ፓርቲ በገለልተኛ የምርጫ አስተዳዳር አማካይነት ገለልተኛ ታዛቢዎች በተገኙበት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ የሆነና ታአማኒነት ያለው ምርጫ ሊካሄድ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከመድረክና ሌሎች ሐቀኛ ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በአስቸኳይ በመደራደር ለነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክርሲያዊና ታዓማኒነት ላለው ምርጫ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠር እንዲደረግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

7ኛ፡- በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንዲረጋገጥ ሕጋዊ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ፣ እንደዚሁም ነፃ ፍትሐዊ ተዓማኒ ምርጫዎች ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይሳተፉ እንቅፋት የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ሁኔታዎችን ለማስወገድ ከኢህአዴግ ጋር የሚካሄድ ድርድርና የሌሎች ድርጅታዊ እንቅስቃሴዎች ውጤት በቀጣዩ ለመድረክ በምርጫዎች መሳተፍ ወሳኝ ይሆናል፡፡ ይህ የሰላማዊ መፍትሔ እርምጃ ከዚህ በፊት በኢህአዴግ አሻፈረኝ ባይነት ተቀባይነት አጥቶ ችግራችን እየተባባሰ እንዲሄድ ሲደረግ እንደቆየው ሁሉ አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጥሎ የሀገራችን ችግሮች እየተወሳሰቡና ከቁጥጥር ውጭ እየሆኑ ከሄዱ ኃላፊነቱ የኢህአዴግ ብቻ እንደሚሆን በቅድሚያ መግለጽ እንወዳለን፡፡

በመጨረሻም ነፃ፣ ፍትሐዊና ታአማኒ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለዘመናት ሲትናፍቅና ስትታገልለት የኖርከው ሰላም ወዳዱ መላው የሀገራችን ሕዝብ መድረክም ሆነ አባል ድርጅቶቹ በኢህአዴግ የ24 ዓመታት አገዛዝ በሀገራችን በተካሄዱት ምርጫዎች በመሳተፍና የሀገራችንን ችግሮች በሰላማዊ ውይይት ለመፍታትና የሕዝባችንን የሥልጣን ባለቤትነት በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማረጋገጥ ባካሄድናቸው ጥረቶች የኢህአዴግን በርካታ የግፍ ተግባራት በከፍተኛ ትዕግሥትና አርቆ አስተዋይነት ተቋቁመህ ከጎናችን በመሰለፍ ላበረከትከው አስተዋዖና ለከፈልከው መስዋዕትነት መድረክ ያለውን ታላቅ አክብሮትና ልባዊ ምስጋናውን ይገልጻል፡፡ የኢህአዴግ አገዛዝ ኃላፊነት በጎደለውና ሕግንና ሕገ-መንግሥትን በጣሰው እርምጃው የነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫን መንገድ ሙሉ በሙሉ በኃይል የዘጋብን ቢሆንም፣ በሀገራችን ሕገመንግሥት የተረጋገጡትና ገና ያልተጠቀምንባቸው የሰላማዊ የትግል ፈርጆች በርካታ ስለሆኑ በሰላማዊ የትግል አማራጫችን ጸንታችሁ አምባገነኑ የኢህአዴግ አገዘዝ ለሕግ የበላይነት እስኪገዛና ሰላማዊ የመፍትሔ ሐሳቦችን ተቀብሎ ሕገመንግሥታዊ መብቶች በተግባር እስኪረጋገጡ ድረስ ሰላማዊ ትግላችሁን ይበልጥ በተደራጃና በተጠናከረ መልኩ እንዲትቀጥሉ መድረክ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ድል ለሕዝባዊ ትግላችን!!

መድረክ
ሰኔ 19 ቀን 2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

Finfinnee, 26 May 2015

Related:

PRESS RELEASE: Amnesty International Asks Ethiopia to Investigate Suspicious Murders and Human Rights Violations

https://oromianeconomist.wordpress.com/2015/06/24/press-release-amnesty-international-asks-ethiopia-to-investigate-suspicious-murders-and-human-rights-violations/

Press release: UK: Minister for Africa expresses concern over Ethiopian elections June 23, 2015

Posted by OromianEconomist in Sham elections.
Tags: , , , ,
add a comment

???????????

Mootummaan Biyya Inglizii flannoo Itopiyaatti ta’e ilaalchisee yaaddoo akka qabu ibse.

The UK: Minister for Africa expresses concern over elections in Ethiopia

Waxabajjii/June 23, 2015 · Finfinne Tribune | Gadaa.com

The following is a press release from the Minister for Africa of the UK government regarding the General Elections of 2015 in Ethiopia. —– Press release Minister for Africa expresses concern over Ethiopian elections UK Minister for Africa James Duddridge Minister for Africa James Duddridge calls on Ethiopian government to increase diversity in parliament and ensure the voices of all citizens are heard. Commenting on the election results, Minister for Africa James Duddridge said: “I welcome the fact that the recent Ethiopian parliamentary elections were conducted in a generally peaceful environment and that the Ethiopian people turned out in large numbers. I agree with European Union concerns about the negative impact on the electoral environment of arrests of opposition members and journalists, closure of media outlets, and obstacles faced by the opposition while campaigning … “In light of the results I urge the Ethiopian government to explore ways to increase the diversity of political parties in future parliaments, and to ensure those who voted for other parties this time still feel their voice is heard in the next five years. I hope that they will comprehensively address all the issues raised in the African Union Election Observation Mission report. The UK stands ready to offer support which might help in this regard.” —- Source: Gov.uk https://www.gov.uk/government/news/minister-for-africa-expresses-concern-over-ethiopian-elections

Power: A curse to a nation but A drug to a Leader May 31, 2015

Posted by OromianEconomist in Colonizing Structure, Corruption in Africa, Sham elections.
Tags: , , , , , ,
add a comment

???????????TPLF in electoral fraud, 24 May 2015Is the age of Africa's political big man nearing an end

Amnesty International: Ethiopia: Onslaught on human rights ahead of elections. #Africa. #Oromia May 23, 2015

Posted by OromianEconomist in Sham elections.
Tags: , , , , , , , ,
add a comment

???????????Because I am Oromo

Ethiopia: Onslaught on human rights ahead of elections

Amnesty International, 22 May 2015

The run-up to Ethiopia’s elections on Sunday has been marred by gross, systematic and wide-spread violations of ordinary Ethiopians’ human rights, says Amnesty International.

“The lead-up up to the elections has seen an onslaught on the rights to freedom of expression, association and assembly. This onslaught undermines the right to participation in public affairs freely and without fear as the government has clamped down on all forms of legitimate dissent,” said Muthoni Wanyeki, Amnesty International’s Regional Director for East Africa, the Horn and the Great Lakes.

The Ethiopian authorities have jailed large numbers of members of legally registered opposition political parties, journalists, bloggers and protesters. They have also used a combination of harassment and repressive legislation to repress independent media and civil society.

The lead-up up to the elections has seen an onslaught on the rights to freedom of expression, association and assembly. This onslaught undermines the right to participation in public affairs freely and without fear as the government has clamped down on all forms of legitimate dissent.
Muthoni Wanyeki, Amnesty International’s Regional Director for East Africa, the Horn and the Great Lakes.

In the run-up to Sunday’s elections, opposition political party members report increased restrictions on their activities. The Semayawi (Blue) Party informed Amnesty International that more than half of their candidates had their registration cancelled by the National Electoral Board. Out of 400 candidates registered for the House of Peoples Representatives, only 139 will be able to stand in the elections.

On 19 May, Bekele Gerba and other members of the Oromo Federalist Congress (OFC)-Medrek were campaigning in Oromia Region when police and local security officers beat, arrested and detained them for a couple of hours.

On 12 May, security officers arrested two campaigners and three supporters of the Blue Party who were putting up campaign posters in the capital Addis Ababa. They were released on bail after four days in detention.

In March, three armed security officers in Tigray Region severely beat Koshi Hiluf Kahisay, a member of the Ethiopian Federal Democratic Unity Forum (EFDUD) Arena-Medrek. Koshi Hiluf Kahisay had previously received several verbal warnings from security officials to leave the party or face the consequences.

In January, the police violently dispersed peaceful protesters in Addis Ababa during an event organized by the Unity for Democracy and Justice Party (UDJ). Police beat demonstrators with batons, sticks and iron rods on the head, face, hands and legs, seriously injuring more than 20 of them.

At least 17 journalists, including Eskinder Nega, Reeyot Alemu and Wubishet Taye, have been arrested and charged under the Anti-Terrorism Proclamation (ATP), and sentenced to between three and 18 years in prison. Many journalists have fled to neighboring countries because they are afraid of intimidation, harassment and attracting politically motivated criminal charges.

Civil society’s ability to participate in election observation has been restricted under the Charities and Societies Proclamation (CSP) to only Ethiopian mass based organizations aligned with the ruling political party.

Amnesty International calls on the Africa Union Election Observation Mission (AU EOM) currently in Ethiopia to assess and speak to the broader human rights context around the elections in both their public and private reporting. It also calls on the AU EOM to provide concrete recommendations to address the gross, systematic and widespread nature of violations of the rights to freedom of expression, association and assembly which have undermined the right to participate in public affairs freely and without fear.

“The African Union’s election observers have a responsibility to pay attention to human rights violations specific to the elections as well as more broadly,” said Wanyeki. “The African Charter on Human and Peoples’ Rights protects the right of Ethiopians to freely participate in their government. This right has been seriously undermined by violations of other civil and political rights in the lead-up to the elections.”

Background

Amnesty International has been monitoring, documenting and reporting on the human rights situation in Ethiopia for more than four decades.

Since the country’s last elections in 2010, the organization has documented arbitrary and politically motivated arrests and detentions, torture and other ill-treatment, as well as gross, systematic and wide-spread violations of the rights to freedom of expression and association.

https://www.amnesty.org/articles/news/2015/05/ethiopia-onslaught-on-human-rights-ahead-of-elections/

Related: AmnestyInternationalReport_BecauseIAmOromo014

Ethiopia: Elections Signal Need for U.S. Policy Change. #Africa. #Oromia May 23, 2015

Posted by OromianEconomist in Sham elections.
Tags: , , , , , , , ,
add a comment

???????????Freedom HouseEthiopia's scores on freedom

Ethiopia: Elections Signal Need for U.S. Policy Change

Freedom House, Washington, May 21, 2015

In advance of Ethiopia’s elections scheduled for May 24, Freedom House issued the following statement and policy recommendations:

“The Ethiopian government’s disregard for international standards for free and fair elections as it prepared for voting should convince the United States that it must rethink and shift its relationship with that government,” said Mark P. Lagon, president of Freedom House. “For Ethiopia to represent a stable, reliable ally in the region, U.S. security and economic assistance must be accompanied by Obama administration strongly urging it take tangible steps to strengthen civil society’s voice, good governance, and democracy.”

Policy Recommendations 

  • Reallocate a portion of the economic and security assistance to programs dedicated to supporting democracy.
  • Push for creation of a special U.S. fund that could become a source of outside support for Ethiopian human rights and democracy groups.
  • Regularly request that visiting U.S. officials obtain access to detention centers where journalists, human rights defenders and other political prisoners are being held.
  • Pursue a strict application of all laws and regulations, including the Leahy Law, that ensure security assistance does not go to perpetrators of human rights abuses.
  • Include in the USAID country development strategy clear guidance on the importance of supporting independent media in Ethiopia, to promote freedom of expression, ensure accountability of government, and fight corruption.

Ethiopia is rated Not Free in Freedom in the World 2015, Not Free in Freedom of the Press 2015, and Not Free in Freedom on the Net 2014.

Freedom House is an independent watchdog organization that supports democratic change, monitors the status of freedom around the world, and advocates for democracy and human rights.

https://freedomhouse.org/article/ethiopia-elections-signal-need-us-policy-change#.VV_c9dJVikp

Oromia: Oromo Federalist Congress’s (OFC/Medrek) Last Campaign Stops – Gujii Zone, Xuquur Incinii (Diree Badhaas) & Holataa Towns and in Bale, Huge Turnouts at Each Stop May 22, 2015

Posted by OromianEconomist in Sham elections.
Tags: , , , ,
add a comment

???????????OFC MEDREK’S Election Symbol (Five Fingers with the Open Palm'High Five Goes Viral1OFC MEDREK’S Election Symbol (Five Fingers with the Open Palm'High Five Goes Viral

OFC/Medrek’s Last Campaign Stops – Gujii Zone, Borana, Xuquur Incinii (Diree Badhaas) & Holataa Towns and Bale, Huge Turnouts at Each Stop

The Oromo Federalist Congress’s (OFC/Medrek) last campaign stops before the upcoming Sunday polls were Gujii, Borana and Bale Zones in southern Oromia, and Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in central Oromia. At each of these campaign stops, OFC/Medrek supporters/voters had come out in huge recording-breaking numbers.

Gujii Zone: Southern Oromia:-

OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Gujii Zone, South Oromia

OFC Supporters/ Voters at Nagallee Borana stadium with Baqqalaa  Nagaa

OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Gujii Zone, South Oromia1

Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa: Central Oromia

Dr. Merera Gudina with his supporters in Xuquur Incinii:

OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia.OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia1OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia2OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia3OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia4

Bale: Southern Oromia

Duulli Filannoo Bara kanaaf gaafa Caamsaa 21 bara 2015 kana Godina Baalee Aanaa Sinaannattii fi Gooroo keessatti Dargaggoonnii fi Maanguddoon Biyyaa Waliin gurma’anii Uummanni Aanaa Kanaa Hubannoo Argatee Koongiresii Federaalawaa Oromoo Akka Filatuuf Magaalaa keessa naanna’anii Sochii guddaa gochaa yoo jiru.

OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Bale, Southern Oromia3

OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Bale, Southern OromiaOFC Medrek’s Last Campaign Stops – Bale, Southern Oromia1

Related:

Video of the OFC/Medrek Naqamtee Campaign with Ob. Bulchaa Dammaqsaa from a Week Ago

OMN regarding the attack on Bekele Gerba

http://www.siitube.com/videos.php?vid=c9565beee

Filannoo Itoophiyaa bara 2015

http://www.voaafaanoromoo.com/content/article/2781344.html

Doorsisi mootummaa qabsoo uummataa hin dhaabsisu jedhu mormitoonni

Ibsa muummicha ministeeraa kanaaf deebii gama mormitootaan deebii kan nuu kennan barreessaa paartii federaalawaa uummata oromoo obbo Baqqalaa Nagaa turan. Uummata keenya qabsoo inni eegale doorsisi mootummaan oofu hin dhaabsisu jedhan.

Waggoota digdamii afuriif uummatichaaf bu’aa hin buusne har’a ka’anii gama misoomaan uummataan fedhii keen guuta jedhanii waadaa duwwaa seenuun waan fakkaatu miti uummatis gowwoomsamaa hin jiru jedhan obbo baqqalaan.

Mootummaan taajjabdoota keenya ka filannoo maqaa isaanii boordii Filannoo irraa guurratee mana hidhaatti naqaa jira, reebaa fi hiraarsaa jira kan jedhan obbo Baqqalaan filannoo taajjabdoota hin qabne geggeessuuf dhiisuu keenya murteessuuf jirra jedhan.

Nuti kan nuti uummataaf waadaa seennu kanaa fi sanan sii godha jennee gowwoomsuu utuu hin ta’ini yoo carraa arganne sirna dimokraasii fi haqaa diriirsuu dhaan uummati keenya jireenya wayyaawaa akka jiraatu gochuuf qabsoofna jedhechuun obbo Baqqalaan nuuf ibsaniiru.

Oromia: SBO: Oduu Filannoo Wayyaanee, Caamsaa 20, 2015 May 21, 2015

Posted by OromianEconomist in Sham elections.
Tags: , , , , , ,
add a comment

???????????sbo

 

Mootummaan Wayyaanee filannoo isaa Caamsaa 24, 2015 Dilbata dhufu geggeeffatuun walqabatee Oromiyaa keessatti iddoowwan Fincilli ummataa ni dhoha jedhee sodaatutti karaa ittiinan dhaamsuu danda’a jedhu humna waraanaatti dabalatee karoora biraa baafatee socho’aa jiraachuun isaa saaxilame.

Filannoon kun filannoo dimokraatawaa, bilisaa fi haqummaa kan hin qabne, ulaagaa filannoo addunyaan beekuu kan hin guutnee fi taajjabdootni idil addunyaa tokkollee kan irratti hin argamne filmaata fakkeessii fi waliin dhahaa tahuun isaa yoo beekamu, mootummaan Wayyaanee filannichaan booda diddaan ummatootaa akka hin dhalanne, addatti ammoo Oromiyaa keessatti Fincilli ummataa fi dargaggootaa ka’uu danda’a sodaa jedhuun diddaa dhalatu dhaamsuuf humna waraanaa, poolisaa fi humnoota tikaa bobbaafatee jirutti dabalee karaa ittiin diddaan kun hin babal’anne tooftaa ittiinan dhaamsa jedhu kan biraa lafa kaawwatee socho’aa jiraachuu Maddeen Oduu SBO saaxilaniiru.

Haaluma kanaan mootummaan abbaa irree fi goolessaan Wayyaanee Oromiyaa keessaa bakkoota fincilli ummataa fi dargaggootaan ka’uu danda’a jedhee sodaataa jiru Dhiha Shawaa, Baha Wallaggaa, Naqamtee fi naannoo ishee, Lixa Wallaggaa D.Doolloo fi naannoo isheetti akkuma adeemsi filannoo xumurameen naannolee kanatti mo’amneerra jedhee labsuun diddaan ummata Oromoo akka hin kaane, bakkoota biraattis fincilli ummataa fi dargaggootaan akka hin qabsiifamne ukkaamsee hambisuuf karoorfatee akka jiru maddeen SBO ifa godhanii jiran.

Filannoo kanaan walqabatee naannolee kanatti mormii ummataa dhalatuu malu tooftaa kanaan ukkaamsinaan bakkoota biratti fincilli hin dhalatu, hin babal’atu, salphaatti filannoo keenya milkii fi injifannoo paartii IHADGn xumurachuu dandeenya jechuun itti amantaan socho’aa jiraachuun isaanii saaxilameera.

Oromiyaa keessattis haa ta’u, naannolee empaayerattii hunda keessatti mootummaan Wayyaanee/IHADG filannoo kana waliin dhahee, korojoo hatee, ummatas doorsisee fi tokko shaneen walitti hidhee akkuma duraanii injifannoo kijibaa labsachuun isaa waan dirree jiru, shakkii tokkollee kan hin qabne ta’uu kan hubachiisan maddeen SBO, karoorri Oromiyaa keessatti fincila ummataa dhaamsuuf Dhiha Shawaa, Baha Wallaggaa, Naqamtee, D.Doolloo fi bakkoota biraatti baafamee jiru kan mul’isu, sagalee ummataa ukkaamsuuf shira olaanaa xaxamaa jiru ta’uun isaa akkuma jirutti ta’ee, mormitootni barcuma lama, shan ykn kudhan argatanii paarlamaa galanii teenyaan isaan gaha jechuu akka ta’e kan mul’isuu dha jedhaniiru.

Kanas ta’e sanas filannoo waliin dhahaa sirna mootummaa Wayyaanee jalatti geggeeffamuun murna shiftaa aangoo humna qawween qabate Wayyaanee aangoo irraa kaasanii sagalee ummataa, waan ummatni fedhu argamsiisuun akka hin danda’amne sabboontotni Oromoo yaada agabaastota SBOf kennaniin mul’isuun, mormitootni maqaa Oromoon jiran barcuma murtooftuu argatanii paarlamaa seenanii taa’uun rakkoo fi gidiraa sirna cunqursaa ummata Oromoo irratti barootaaf jiraate furuu akka hin dandeenye, kaleessas akka hin danda’amiin addeessaniiru.

Kanaaf ummatni Oromoo, ka’imman Oromoo waca filannoo kanaan dahatee deemaa jiruun osoo hin dagamne, keessaa fi alatti irree isaa gamteeffachuun bilisummaa fi mirga abbaa biyyummaa isaa dhugoomfachuuf qabsoo isaa caalaatti jabeeffatee, FDG bifa gara garaan deemaa jirus daran babal’isee finiinsuu akka qabu sabboontotni Oromoo dhaamsa isaanii dabarsanii jiru.

Addi Bilisummaa Oromoo (ABO)n filannoo Wayyaanee kana ilaalchisuun ibsa Caamsaa 18,2015 baaseen, Filannoon Caamsaa 24, 2015nitti baallamamee jiru Wayyaanee aangomsuun alatti faydaa biraa ummatootaaf argamsiisu tokkollee akka hin qabne ifa gochuun, ummatni Oromoo haqa kana hubatuun furaan dhibdee isaa qabsoon malee kan hin argamne tahuu beekee, filannoo kijibaan akka hin dagamne, mirgaa fi bilisummaa isaa qabsoo isaan gonfachuuf jabaatee akka warraaqu ibsa kanaan yaamicha isaa dabarsee jira.

http://gadaa.net/FinfinneTribune/2015/05/sbo-oduu-filannoo-wayyaanee-caamsaa-20-2015/

ETHIOPIA: Political Violence Intensifies as the fifth Sham Election Approaches February 17, 2015

Posted by OromianEconomist in Knowledge and the Colonizing Structure. African Heritage. The Genocide Against Oromo Nation, The Tyranny of TPLF Ethiopia.
Tags: , , , , ,
add a comment

???????????

HRLHA FineHRLHA Urgent Action

February 16, 2015

According to a schedule released by the National Electoral Board of Ethiopia, citizens will go to the polls to elect a new government on 24 May 2015. It will be Ethiopia’s fifth national election since EPRDF came to power in 1991.

In connection with the coming National Election of Ethiopia, the ruling EPRDF government has begun to wage a widespread campaign to secure again the 99.6% of parliamentarian seats it has controlled since 2010- the seats it acquired by electoral fraud.  As the election date of May 2015 approaches, the government of Ethiopia has unabashedly continued its systematic violence against opposition political parties’ leaders, members, and supporters.  Candidates of the opposition political parties are the major targets in all regional states in the country including the capital city, Finfinne/Addis Ababa.    For example, the information that the HRLHA has obtained through its correspondents indicates that hundreds of election candidates of the opposition OFC (Oromo Federalist Congress) party from most zones of Oromia Regional State have been arrested and sent to prisons.

In the most recent wave of arrests and imprisonments that has been going on since the first week of January, 2015 and which has touched almost all corners of Oromia, hundreds of OFC party leaders, members and supporters from all walks of life have been taken from their homes and work places and sent to prison.

According to the HRLHA reporter, in this particular political violence by the ruling party against the OFC party leaders, members and supporters in western Oromia zone Qellem, Dabidolo and Gambit districts, in the eastern Wallagga zone Guduru, Nunu Qumbq, and Wama Haagaloo districts, in the Eastern Oromia Zone in the Western Hararge zone in Masala district, in the Southern Oromia zone in Robe – Bale town Regional State of Oromia have been taken to prison.

The HRLHA reporter has managed to obtain the names of the following few OFC leaders   currently held in prison: 1, Mr. Dula Maatiyoos, chairman of the OFC political party in Qelem district, 2. Mr. Abiyot Tadesse, Chairman of the OFC political party in Dambi Dollo district, 3. Mr Zelalam Shuma, chairman of the OFC political party in Sayyo district, and 4. Mr. Mezgebu Tolessa, chairman of the OFC in Gidami district.

The HRLHA strongly condemns the EPRDF government’s move towards the systematic elimination of the opposition parties from the coming election in order to control again all parliamentarians’ seats for itself as has happened in the previous four elections. It should be remembered that the EPRDF has claimed victory in the elections of 1995, 2000, 2005 and 2010- ever since the fall of the military/ Derg regime of 1991 and the adoption of a new constitution in August 1995.

The HRLHA calls on the Western allies of the ruling TPLF/EPRDF party as well as regional and international diplomatic, development and donor agencies to put pressure on the Ethiopian government and demand an immediate halt to this extra-judicial and unconstitutional act of violence and the unconditional release of those innocent citizens whose arrests and imprisonment are purely political. It also calls on those bodies to put additional pressure on the ruling TPLD/EPRDF party to organize a truly free and fair election, and prepare itself to participate accordingly.

This UA is copied to:

 Current Membership of the Human Rights Council

 Office of the UN High Commissioner for Human Rights
United Nations Office at Geneva 1211 Geneva 10, Switzerland Fax: + 41 22 917 9022 (particularly for urgent matters) E-mail: tb-petitions@ohchr

 Human Rights Treaties Division (HRTD)
Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR)
Palais Wilson – 52, rue des Pâquis
CH-1201 Geneva (Switzerland)
Tel.: +41 22 917 97 06
Fax: +41 22 917 90 08
E-mail: cat@ohchr.org

 Secretariat contact details
Secretariat of the Subcommittee on Prevention of Torture
Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR)
Palais Wilson – 52, rue des Pâquis
CH-1201 Geneva (Switzerland)
Mailing address
UNOG-OHCHR
CH-1211 Geneva 10
Switzerland
Tel: +41 22 917 97 44
Fax: +41 22 917 90 22
E-mail: opcat@ohchr.org
Internet: http://www.ohchr.org

 Committee on Enforced Disappearance (CED)
Human Rights Treaties Division (HRTD)
Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR)
Palais Wilson – 52, rue des Pâquis
CH-1201 Geneva (Switzerland)
Mailing address
UNOG-OHCHR
CH-1211 Geneva 10 (Switzerland)
Tel.: +41 22 917 92 56
Fax: +41 22 917 90 08
E-mail: ced@ohchr.org

 Office of the UNHCR
Telephone: 41 22 739 8111
Fax: 41 22 739 7377
Po Box: 2500
Geneva, Switzerland

 African Commission on Human and Peoples‘ Rights (ACHPR)
48 Kairaba Avenue, P.O.Box 673, Banjul, The Gambia.
Tel: (220) 4392 962 , 4372070, 4377721 – 23 Fax: (220) 4390 764
E-mail: achpr@achpr.org
• Office of the Commissioner for Human Rights

 Council of Europe
F-67075 Strasbourg Cedex, FRANCE
+ 33 (0)3 88 41 34 21
+ 33 (0)3 90 21 50 53

 U.S. Department of State
Short Echalar Julie A
shortJA@state.gov

 U.S. Department of State
Trim, Vernelle X
Ethiopian desk officer
trimvx@state.gov

 Amnesty International – London
Claire Beston
Claire Beston” <claire.beston@amnesty.org>,

 Human Rights Watch
Felix Hor
“Felix Horne” <hornef@hrw.org>,