jump to navigation

Statement from Oromo Federalist Congress: የታሪክ ሽሚያ ለማካሄድ ካልሆነ በስተቀር የእሬቻ ሰማዕታት ፓርክ/ሐዉልት በተጠያቂዎች ሊቆም አይገባም፤ በመሬት ጥያቄ ምክንያትም የሰዉ ሕይወት አይቀጠፍም፡፡ September 7, 2017

Posted by OromianEconomist in OFC, Uncategorized.
Tags: , , , , , , , ,
add a comment

 

 

Odaa Oromoooromianeconomist

Oromo Federalist Congress Statement on 7  September  2017, page1.png

Oromo Federalist Congress Statement on 7  September  2017, page2.png

 

የታሪክ ሽሚያ ለማካሄድ ካልሆነ በስተቀር የእሬቻ ሰማዕታት ፓርክ/ሐዉልት በተጠያቂዎች ሊቆም አይገባም፤ በመሬት ጥያቄ ምክንያትም የሰዉ ሕይወት አይቀጠፍም፡፡


ከኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ የተሰጠ መግለጫ


መስከረም 22 ቀን 2009 የእሬቻን ባህላዊና ሃይማኖታዊ በዓል ለማክበር በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ በተሰባሰቡ የኦሮሞ ዜጎች ላይ ሆን ተብሎ በተወሰደ የመንግስት ያልተገባ እርምጃ የብዙ ዜጎች ሕይወት ተሰዉቷል፡፡ አስቀድሞ ሲደረጉ የነበሩ ዝግጅቶች አደጋ ሊያስከትሉ እንደሚችሉ በመጠርጠር ፓርቲያችን፤ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ “የእሬቻ በዓል የሕዝብ ባህልና ሃይማኖት በጣምራ የሚከበርበት መሆኑ ታዉቆ ማናቸዉም የፖለቲካ ኃይሎች ከዋዜማዉ ጀምሮ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አበክረን እናሳስባለን፡፡” የሚል መግለጫ መስከረም 10/2009 ማዉጣታችንን እናስታዉሳለን፡፡
የሰጠነዉ ማሳሰቢያ የመንግስት ባለሥልጣን ሰሚ ጆሮ ባለማግኘቱና ቀደም ሲልም በሕዝብና በገዥዉ ፓርቲ መሀከል የነበረዉ መልካም ያልሆነዉ ግንኙነት ፈጦ ሊወጣ በመቻሉ በተለይም ወጣቱ የተቃዉሞ ድምፅ በማሰማቱ የመንግስት ኃይሎች በታዘዙት መሠረት የኃይል እርምጃ ወስደዋል፡፡ በዚህም የተነሳ ጥቂት በሚባሉ ወጣቶች የተቃዉሞ መፈክር ማንሳት የተነሳ፤ የመንግስት ኃይሎች ኃላፊነት በጎደለዉ ሁኔታ እጅግ ብዙ ሆኖ በተሰበሰበዉና ምንም ማምለጫ መንገድ በሌለዉ ንጹኃን ሕዝብ ላይ የኃይል እርምጃ ተወስዷል፡፡ በዚያ ዓይነት ሁኔታ በሕዝብ ላይ የበቀል እርምጃ መዉሰድ እጅጉን የሚከብድ መሆኑ ማመዛዘን ለሚችል ሰዉ የሚከብድ መሆኑ እየታወቀ፤ ከአቅም በላይ የሆነ እርምጃ በመወሰዱ የብዙ ዜጎቻችን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አልፏል፡፡

የዚህ መግለጫ አስፈላጊነት ደግሞ እነዚያን በግፍ የተገደሉ ዜጎችን ለማስታወስ ሲባል የመታሰቢያ ፓርክ የሚባል ተገቢ ባልሆነ ቦታ ላይ ተገቢ ባልሆነ አካል መሰራቱ ነዉ፡፡ በወቅቱ የተገደሉ ዜጎች ተለይተዉ መላዉ ሕዝብ ባላወቀበትና በገለልተኛ አካል ተጣርቶ በኦሮሞ ሕዝብ ደንብ መሠረት ጉማ ወይም የደም ካሳ ባልተከፈበት ሁኔታ ዉስጥ ሆኖ፤ ገዳዮችና አዛዦቻቸዉ ለፍርድ ሳይቀርቡ ፓርክ ተሰራላቸዉ ሲባል የሟች ቤተሰቦችም ሆኑ መላዉ ሕብረተሰባችን የሚቀበሉት አይደለም፡፡ ምክንያቱ ቀላል ነዉ፡፡ የሰማዕታት ሐዉልትም ሆነ የመታሰቢያ ፓርክ በተጠያቂዎች አይገነባም፡፡ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስትም ሆነ ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት የሚጠበቅ ነገር ቢኖር የሟቾችን ማንነት በገለልተኛ አካል ይፋ ማድረግ፣ ጉማ ወይም የደም ካሳ መክፈልና ገዳዮችን ለፍርድ ማቅረብ ነዉ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ተሰራ የተባለዉ የመታሰቢያ ፓርክም ዜጎቹ ከተገደሉበት ቦታ ርቆ መተከሉ የግብር ይዉጣ ሥራ ከመሆኑም በላይ የታሪክ ሽሚያ ለማካሄድ ካልሆነ በስተቀር የእሬቻ የሰማዕታት ሐዉልትም ሆነ ፓርክ በተጠያቂዎች ሊቆም አይገባም እንላለን፡፡ በሌላም በኩል ሕብረተሰቡ እነዚህ የተሰዉ ወገኖች በጥልቅ ሐዘን የሚያስታዉሳቸዉ ከመሆኑም በላይ ስማቸዉንና ምስላቸዉን በዝርዝር ማስቀመጥ ሲገባ እንዲሁ አንድ ቁም ድንጋይ ተክሎ ከጉዳዩ ጋር የማይመስለዉን ሀተታ በጽሑፍ ማስቀመጡ አሳዝኖናል፡፡ ከዚህ ጋርም በፓርኩ የመግቢያ በር ላይ በአፋን ኦሮሞ ተጽፎ የሚገኘዉ “Paarkii Yaadannoo Namoota Ayyanaa Irreechaa Irratti Lubbuun Isaani Tasa Darbe Yaadachuuf Moggaafame” የሚለዉ ዜጎቹ የሞቱት በድንገተኛ ሁኔታ እንደሆነ በጽሑፍ ማስቀመጡ በኦሮሞ ዜጎች መስዋዕትነት ላይ የማፈዝ ያህል ስለሆነ ተጨማሪ የሕዝብና የመንግስት ግጭትን ሳይጋብዝ ከቦታዉ እንዲነሳ እንጠይቃለን፡፡

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከኦሮሚያ ክልል ላይ የድንበር ጥያቄ የሚያነሱና በድንበሮች አካባቢ በሚገኙ የኦሮሞ ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ ኃይሎች ጉዳይ ከአሳሳቢ ደረጃም ያለፈና የዜጎቻችንን ሕይወት እየቀጠፈ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ ይህ የመሬት ጥያቄ የድንበር አከባቢ ሕዝቦችን በማጋጨት ከፍተኛ የሕይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ ይገኛል፡፡ የመሬት ጥያቄዉን አንዳንዴ ሲመለከቱት ኢትዮጵያዊያን በቀጣይ ጊዜያት ዉስጥ አብሮ የመኖር ዕጣ ፋንታቸዉ እያበቃ ያለ ያስመስላል፡፡ ምክንያቱም በምዕራብ፣ በደቡብ ምዕራብና በምስራቅ ኦሮሚያ በኩል የሚገኙት የገዥዉ ፓርቲ ካድሬዎችና ካቢኔዎች የሕዝቦች አብሮነት እንዲያከትም ፍላጎት ያላቸዉ ይመስላሉ፡፡

በድንበር አከባቢ የሚኖሩ ሕዝቦች በግጦሽ ሳር፣ በኩሬ ዉሃ፣ በጠፈ ከብትና በጥቃቅን ነገሮች ሊጋጩ እንደሚችሉና በአከባቢ ሽማግሌዎችና በጎሳ መሪዎች አማካይነት ሊታረቁ እንደሚችሉ፤ እነዚህ የአገር ሽማግሌዎችና የጎሳ መሪዎች ችግሮችን ሲፈቱም እንደነበረ ይታወቃል፡፡ የመሬት ወረራዉና የሰዎች ግድያዉ የኦሮሞን ሕዝብ ቁጥርና የኦሮሚያን የቆዳ ስፋት ለማሳነስ ታቅዶ የተቀመጠዉን እስትራቴጂ ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ ያለ ይመስላል፡፡ በተለይም በምስራቅ ኦሮሚያ በኩል በሱማሌ ልዩ ኃይል በኦሮሞ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት እጅጉን ያሳስበናል፡፡
ስለሆነም እንደዚህ ዓይነት የጥቃት እርምጃዎች ለወደፊቱ ኢትዮጵያዊያን አብሮነት የማይፈይድና ወቅትን እየጠበቀ የሚፈነዳ ፈንጂ እየሆነ ስለሚቀጥል የሚመለከታቸዉ የመንግስት አካላትና ሕብረተሰቡ አስፈላጊዉን የዕርምት እርምጃ እንዲወስዱ አበክረን እናሳስባለን፡፡

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ
ፊንፊኔ፤ ጳጉሜን 2/2009

Oromia: Paartiileen Mormiitoota Itoophiyaa, Obaamaa komatan. July 28, 2015

Posted by OromianEconomist in OFC.
Tags: , ,
add a comment

???????????OFC Medrek’s Last Campaign Stops – Xuquur Incinii (Diree Badhaas) and Holataa in Central Oromia4OFC MEDREK’S Election Symbol (Five Fingers with the Open Palm'High Five Goes ViralOFC criss crossing Oromia ,  Shashe Town,  9 May 2015

(OMN:Oduu Adol.27, 2015) Ameerikaan Rakkoo sabaaf utuu hin taane sodaa ofii isheef qabdu irraa kaatee Mootummoota abbaa irreef beekamtu kennuu akka barbaaddu Dr Mararaa Guddina himan.

Dura taa’aan Paartii Samayaawwii Injinar Yilkal Getnat affeerraa Irbaataa Pirzdant Omaaf qophaa’e irratti akka hin argamne beeksisan.

Dura taa’aa Itti aanaan paartii Madrak Dr Mararaa Guddinaa akka himanitti daawwiin Pirezdant Obaamaan Itoophiyaatti gochaa jiran gaaffii fi bu’aa ummata Itoophiyaaf utuu hin taane dhimmonni shororkesummaa gaanfaa Afriikaa waan Amerikaa irriba dhorkateef jedhan.

Ameerikaa Xiyyaara waraanaa nama malee balali’u Drone jedhamu Nannoo Arbaa Mincii akka qabdu fi Itoophiyaan Soomaliyaa keessatti ergama Ameerikaa waan raawwachaa jirtuuf obamaan dhimma kana cimsuuf akka achi deeme dubbataniiru.

Itoophiyaa keessatti Ijaarsa sirna dimookiraasii babalisuuf Pirezdant Obaamaan miillaan dhufu hin barbaachisu ture kan jedhan Dr Mararaan Pirezdantiin wagga tokko booda aangoo isaa iyyuu gad dhiisuuf jiru jijjirama gudda siyaasa Itoophiyaa keessatti fida jedhanii akka hin yaadnes himan.

Gama biraatiin dura taa’aan Paartii Samayaawwii Injinar Yilkal Getnat affeerre Irbaataa Pirzdant Omaaf qophaa’e irratti akka hin argamne beeksisan.

Injinar Yilkaal Gaazexxa Nagara Itoophiyaaf ibsa kennaniin Pirzdant Baraak Obamaan Ihadeg Paartii karaa dimokiraasiitiin filatame jechuun isaanii ijaarsa sirna Dimookiraasii Itoophiyaa irratti bishaan naquu dha jedhan.

Waamicha aaffeerraa Irbaataa Ihadeg Waame irratti argamuun dararaa fi miidhaa ummata ofii irra gahaa jiru akka irraanfachuuttan ilaalaa jechuun yaadasaanii nuuf kenannii jiru.

Mootummaan Itoophiyaa paartiilee Mormitootaa akka shororkesitootatti ilaaluy prezdant Baraak Obamaan dhufnaan akka paartii karaa seera qabeessaa filatameetti of fakkeessuuf waamicha taasise waan ta’eef irartti hirmaachuu dhiisuuf murteessera jedhan.

Ibsi Pirezdant Obaamaan Mootummaa karaa Dimokiratawaa fialtame jechuun kennanis akka isaan gaddisiisse himuun Ihadeg karaa Dimookiratawaa filatame jedhanii beekmatii kennuun paartiilee karaa nagaa qabsaaaniif dantaa dhabuu akkasumas Mootummaa abbaa irreetiif deggersa kennu ta’aa jechuun dubbii Obamaa qeeqaniiru.

Gabaasaan Alamaayyoo Qannaa ti.

https://www.oromiamedia.org/2015/07/paartiileen-mormiitoota-itoophiyaaobaamaa-komatan/

Oromia & Ethiopia: Flannoo kijibaa Wayyaanee Caamsaa Darbee Ilaalishisee Ibsa OFC/Medrek: OFC/Medrek’s Statement Regarding Ethiopia’s May 2015 Sham Election June 27, 2015

Posted by OromianEconomist in OFC, Sham elections.
Tags: , , , , ,
add a comment

???????????OFC MEDREK’S Election Symbol (Five Fingers with the Open Palm'High Five Goes Viral

Deja vu in 2015 Ethiopian Elections

በ2007 በኢትዮጵያ የተካሄደውን ምርጫ በሚመለከት ከመድረክ የተሰጠ መግለጫ:- ሕገ-መንግሥታዊና ሕጋዊ የምርጫ ሥርዓት በተጣሰበት ሂደት የተከናወነው ሕገ ወጥ የምርጫ ድራማ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም!

ከመድረክ የተሰጠ መግለጫ …

ሕገ-መንግሥታዊና ሕጋዊ የምርጫ ሥርዓት በተጣሰበት ሂደት የተከናወነው ሕገ ወጥ የምርጫ ድራማ ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም!

በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እውን ሆኖ በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ አማካይነት የሕዝባችን የሥልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጥበት ሁኔታ በሕገ-መንግስቱ እውቅና ተሰጥቶት በይፋ ተደንግጎአል፡፡ ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ሕገመንግሥቱንና የምርጫ ሕጎችን የጣሰ የምርጫ ድራማ በየ5 ዓመቱ በመቶ ሚሊዮኖች የሀገር ገንዘብ እያባከነ ያካሂዳል፡፡ ኢህአዴግ ይህንን የምርጫ ድራማ የሚያከሂደው፣ ወቅቱን የጠበቀ ምርጫ ማካሄድ በዓለም አቀፍ ለጋሽ ዴሞክራሲያዊ ሀገሮች ዘንድ እውቅና የስገኝልኛል በሚል ተስፋ ነው፡፡ ተጨባጩ እውነታ የሚያሳየው ግን ኢህአዴግ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው 24 ዓመታት ራሱ ያጸደቃቸውን ሕጋዊና ሕገመንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በመርገጥ የራሱን አምባገነናዊ ገዥነት ለማስቀጠል እንዲያስችለው የሕዝብ ድምፅ መንጠቂያና ማፈኛ ሕገወጥ የምርጫ ስትራቴጂዎችን እያወጣና ሥራ ላይ እያዋለ መሆኑን ነው፡፡ የሕዝባችንን ድምፅ መቀማቱንና ማፈኑን በየምርጫ ዙሮቹ እያባባሰ መሄዱን ቀጥሎበት አሁን ለደረስንበት የ100 ፐርሰንት ቅሚያም ደርሶአል፡፡ በተለይም በ2007 ዓም በተካሄደው የ5ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ሕጋዊና ሕገመንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በማንአለብኝነት በመጣስ በአጋርነት የፈረጃቸውን ፓርቲዎች አስከትሎና ሕዝቡንና ሐቀኛ ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በኃይል አፍኖ ምርጫውን በሕገወጥ መንገድ መቶ በመቶ ለመቆጣጠርና ጠቅልሎ ለመውሰድ የፈጸማቸው አስነዋሪ ተግባራት ከአንድ በመንግሥት ኃላፊነት ላይ ከሚገኝ ፓርቲ የማይጠበቁ ናቸው፡፡ አገዛዙ በዚሁ ምርጫ ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ ከፈጸማቸው ሕገወጥ ተግባራት ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

1ኛ፡- የኢህአዴግ ካድሬዎች ከምርጫ ቦርድ በሚደረግላቸው ትብብር ብዛት ያላቸው የመራጮች ምዝገባ ካርደ እየተሰጣቸው አህአዴግን ይመርጣሉ ለሚሏቸው ቤት ለቤት በመዞር ለአንድ ሰው ከአስር ካርዶች በላይ ከተለያዩ ማስፈራሪያዎችና መደለያዎች ጋር ጭምር የምርጫው ዕለት ድረስ በማደል አንድ ሰው አንድ ድምጽ የሚለውን ሕግ በመጣስ ወንጀል ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡ ተቃዋሚዎችን ይመርጣሉ ብለው የጠረጠሩዋቸውን በርካታ ዜጎችንም የምርጫ ምዝገባው ጊዜ ከማለቁ በፊት በምርጫ አስፈጻሚዎች #መዝገቡ ሞልቷል$ ወይም #ካርዱ አልቋል$ እየተባለ ሳይመዘገቡ እንዲቀሩ ተደርጓል፡፡ እንደዚሁም መድረክ በመረጃ የደረሰባቸውን ለሰው የታደሉ ትርፍ የመራጭ ካርዶችን ከመራጮች ምዝገባ ላይ ለማመሳከር ባደረገው ጥረት ካርዶቹ ተመዝግበው ያለመገኘታቸውን ማረጋገጡ፣ በመራጮች ምዝገባ ሂደት ከፍተኛ ወንጀል እንደተፈጸመ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አዋጅ 532/1999፣አንቀጽ 65 3ለ ላይ የሰፈረውን #እያንዳንዱ መራጭ በመራጮች መዝገብ ላይ ስሙ ሰፍሮ መገኘት አለበት$ የሚለውን ድንጋጌ መጣሱም ምርጫውን ሕገወጥ የሚያደርግ ነው፡፡

2ኛ፡- በየምርጫ ጣቢያዎቹ የሕዝብ ታዛቢዎች ተብለው የተሰየሙት ሰዎችም የምርጫ ደንብ በሚያዘው መሠረት፣ በምርጫ የሚወዳደሩ ፓርቲዎች በደብዳቤ ተገልጾላቸው ተወካዮቻቸው በተገኙበት መመረጥ ሲገባቸው ያለተቃዋሚ ፓርቲዎች ተሳትፎ በአህአዴግ ደጋፊነታቸው የተመለመሉ መሆኑ ምርጫው ነፃና ታአማኒ እንዳይሆን ከመነሻው የተወጠነ ሕገወጥ አካሄድ ነበር፡፡

3ኛ፡- ገዥው ፓርቲ መንግሥታዊ ሥልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም በየክልሉ የመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር ሕግ የተፈቀደውን የቅስቀሳ ጊዜ ፈቃድ ለመድረክ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ከልክሎ የኢህአዴግ አባላት የሆኑ ከፌዴራል እሰከ ወረዳ ደረጃ ያሉት እጅግ በርካታ የመንግሥት ሠራተኞች ዕጩ ተወዳዳሪ ያልሆኑት ጭምር ከሙሉ ክፍያ ጋር ከመደበኛ ሥራቸው ነፃ ሆነው በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት በየተወለዱበት ወረዳዎችና ቀበሌዎች ተሠማርተዋል፡፡ ለምርጫ የተመዘገበውን ሕዝብም ቤት ለቤት እየዞሩ በማስፈራራትና በመደልል የንብ ምልክት ብቻ እንዲመርጡና መምረጣቸውንም ለኢህአዴግ ተወካዮች በግልጽ እያሳዩ ኮሮጆ ውስጥ እንዲጥሉ፣ ይህንን ካላደረጉ ግን ተቃዋሚዎችን እንደመረጡ እንደሚቆጠርና ተለይተውም እንደሚታወቁ በማስጠንቀቅና በማስፈራራት ላይ ተሰማርተው ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ ሕገወጥ ሥራ የተሰማሩት የኢህአዴግ አባላት የሆኑት የመንግሥት ሠራተኞች በብዙ አከባቢዎች የመንግሥት ተሸከርካሪዎችን ለምርጫ ቅስቀሳ በማንአለብኝነት ሲገለገሉበት ቆይተዋል፡፡

4ኛ፡- በምርጫው ሂደት በብዙ ምርጫ ክልሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የመድረክ ዕጩዎችና ቀስቃሾች ሲደበደቡና ከባድ ጉዳት ሲደርስባቸው፣ ሲታሰሩና ለቅስቀሳ የሚጠቀሙባቸውን መሳረያዎች በገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ሲነጠቁና ሲቀሙ ቆይተዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በዳራሞሎ ወረዳ 26፣ በዛለ ወረዳ 19፣ በካምባ ወረዳ 4፣በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ 2፣ በኦሮሚያ ክልል በባሌ ዞን ዶሎ መና ወረዳ 40፣ በቦረና ዞን ቡሌ ሆራ ወረዳ 40፣ በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦና ጀልዱ ወረዳዎች 27፣ በትግራይ ክክል በመቀሌ ከተማ 17 ፣ እስከአሁን በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን በመቶዎች የሚቆጠሩት በዋስ ተፈትው ጉዳያቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡

5ኛ፡- የዜጎችን ነፃና ምስጢራዊ የድምፅ አሰጣጥ መርሕ በመጣስ አንድ አባል 11 መራጮችን መልምሎ እንዲከታተልና ሕዝቡ በ1ለ5 ተጠርንፎ እስከ ምርጫ ጣቢያዎች ድረስ ተያይዞ በመሄድ ድምፅ እንዲሰጥ በገዥው ፓርቲ በተቀየሰው ስተራቴጂ ምርጫው እንዲካሄድ ተደርጓል፡፡ በአከባቢው በሌሉና በማይታወቁ ሰዎች ስምም የተመዘገቡ ካርዶችን በመጠቀም ምርጫው እንዲካሄድ አድርገዋል፡፡ ለምሳሌም በደቡብ ክልል በቀድዳ ጋሜላ ወረዳ ይህ ተፈጽሟል፡፡

6ኛ፡- በምርጫው ዕለት በአብዘኛው ምርጫ ጣቢያዎች የመድረክ ተወካዮች እንዳይገኙ በማባረር፣ በመደብደብና በማሰር ምርጫውን ታዛቢዎቻችን በሌሉበትና የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሆኑት የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ አመራር አባላት የምርጫ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠሩበትና አዋጅ ቁጥር 532/1999 አንቀጽ 47 ንዑስ አንቀጽ 3 በመተላለፍ ልዩ ኃይል ፣የፌዴራል ፖሊስና ታጣቂዎችን በሕዝቡ መካከል በብዛት በማሰማራት በህዝቡ ላይ የሥነ ልቦና ሽብር በፈጠሩበት ሁኔታ ምርጫው ሊካሄድ ችሎአል፡፡ ብዙ የምርጫ ጣቢያዎችንም በርካታ ታጣቂዎች ልዩ ትጥቅ አንግበው እንዲቆጣጠሩት ተደርጓል፡፡ ከበርካታ ምርጫ ጣቢያዎችም በየጣቢያዎቹ ተገኝተው የነበሩት ወኪሎቻችን እየተፈጸሙ ያዩትን የምርጫ ሕግ ጥሰቶች ለማሳረም ሲሞክሩ ተደብድበው ተባረዋል፡፡

7ኛ፡- በበርካታ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ሰነዶች፣ የድምፅ መስጫ ወረቀቶች የምርጫ ጣቢያ የኮድ ማሕተሞችና የኮሮጆ ቁልፎች በሥርዓት ባልተያዙበትና ኮሮጆዎቹ ቀድመው ሞልተው ባደሩበት እንደዚሁም አዲስ የመራጭ ካርድም በአዲስ መልክ ሲታደል በነበረበትና የንብ ምልክት የተደረገባቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ከውጭ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየገቡ ጥቅም ላይ ሲውሉ በነበረበት ሁኔታ የድምፅ አሰጣጡ ተከናውኖአል፡፡

8ኛ፡- ለመድረክ ድምፅ የተሰጠባቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች በብዛት ሽንት ቤት የተጣሉበትና የተቃጠሉበት ሁኔታ በብዙ አከባቢዎች ተከስቶአል፡፡ ለዚሁም ማስረጃ የሚሆኑ በርካታ ከሽንት ቤት የተሰበሰቡ ድምጾች ለአብነት በእጃችን ይገኛሉ፡፡

9ኛ፡- የመራጭ ምዝገባ አፈጻጸም መመሪያ 2/2000፣ አንቀጽ 13/7 # በአንድ ድምፅ መስጫ ጣቢያ ከ1000 በላይ ድምፅ አይሰጥም$ የሚለውን ድንጋጌ በመተላለፍ የኢህአዴግ ተወዳዳሪዎች ከ1000 በላይ ድምጽ እንዳገኙ ተደርጎ ይፋ መደረጉና ይህ እየታወቀ በምርጫ ቦርድም የእርምት እርምጃ አልተወሰደም፡፡

10ኛ፡- በቅድመ ምርጫም ሆነ በምርጫው ዕለት የተከሰቱ የሕግ ጥሰቶችና የኃይል እርምጃዎችን በሚመለከት መድረክ ከምርጫ ጣቢያዎች አንስቶ እስከ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ድረስ ላሉት አካላት ያቀረባቸው ቅሬታዎችና አቤቱታዎች ተገቢው መፍትሔ ሳይሰጣቸው ቀርቶ ችግሩ እየተባባሰ ገዥው ፓርቲ በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት በመመራት የታጠቀ ኃይል በሰላማዊ ሕዝብ ላይ በማዝመት ጭምር ያከናወነው ምርጫ ሊሆን ችሎአል፡፡

11ኛ፡- በምርጫው ዕለት በኦሮሚያ ክልል በምራብ ሸዋ ዞን ሚዳ ቀኝ ወረዳ በአቶ ጊዲሳ ጨመዳ እና በምዕራብ አርሲ ዞን በቆራ ወረዳ በአቶ ገቢ ጥሴቦ ላይ ግድያዎች የተፈጸሙ ሲሆን፣ ከምርጫው በኋላም በምራብ ትግራይ ዞን በማይካድራ ከተማ በአቶ ታደሰ አብርሃና በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል በሀዲያ ዞን በሶሮ ወረዳ በአቶ ብርሃኑ ኤረቦ በሚባሉ በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳትፎ ባደረጉት የመድረክ ሰላማዊ ታጋዮች ላይ አሰቃቂ ግዲያዎች ተፈጽመዋል፡፡ በጋሞጎፋ ዞን በአርባ ምንጭ ምርጫ ክልልም በምርጫው እንቅስቃሴ ጠንካራ ተሳትፎ ባደረገውና በላካ ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ የመድረክ ወኪል/ታዛቢ በነበሩት በአቶ ዳንኤል ጉዴ ላይ በተደረገው የመግደል ሙከራ ከቤተሰባቸው ጋር እቤት ውስጥ ተኝተው እያሉ ቤታቸውን ከውጭ በገመድ አስረው በእሳት በማቃጠል ከነቤተሰባቸው ለመጨረስ ሙከራ የተደረገ ሲሆን የመድረክ አባሉና ቤተሰቡ በጎረቤት እርዳታ ሕይወታቸው ሲተርፍ ቤት ንብረታቸው በሙሉ ተቃጥሎ በአሰቃቂ ሁኔታ ሜዳ ላይ ቀርተው ይገኛሉ፡፡ የሰላም ታጋዩ በአሁኑ ወቅት ከቀበሌአቸው በኢህአዴግ ካድሬዎች የተባረሩ ሲሆን ከአቅመደካማና ቤቱ ከመቃጠሉ በፊት በካድሬዎቹ ክፉኛ ከተደበደቡት አሮጊት እናታቸው ጋር ወደ ቀበሌአቸውም እንዳይመጡ በካድሬዎች ተከልክለው እየተንከራተቱ ይገኛሉ፡፡

12ኛ፡- ከዚህ በላይ በአጭሩ ለመግለጽ በተሞከረበት ሁኔታ በምርጫው የሕዝቡን ድምፅ ጠቅልለው የወሰዱት የኢህአዴግ ካድሬዎች ይህ አስነዋሪ ተግባራቸው አልበቃ ብሎ ከምርጫው ማግስት ጀምረው በብዙ አከባቢዎች #ለመድረክ በታዛቢነት አገልግላችኋል፣ሕዝቡ መድረክን እንዲመርጥ ቅስቀሳ አድርጋችኋል፣ መድረክን መርጣችኋል$ ወዘተ ባሉዋቸው በርካታ ዜጎች ላይ የበቀል እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚሁም መሠረት በተለያዩ አከባቢዎች በርካታ አባሎቻችንን በማሰር፣ በመደብደብ፣ ቤታቸውን በማፍረስና በሐሰት ወንጅሎ በማስቀጣት፣ ከሥራቸውና ከትምህርት ገበታቸው በማባረር፣ የሥልጠና ዕድል በመንፈግና በመንግሥት ሥራ እንዳይቀጠሩም በመከልከል እንደዚሁም በገጠር በግብርና ሥራ ላይ የተሰማሩ አባሎቻችን የሰፍትኔት ዕርዳታና ሌሎች መንግሥታዊ እርዳታዎችንና አገልግሎቶችን እንዳያገኙ በማድረግ ወዘተ የዜግነት መብታቸውን ነፍገው እያሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቻችንንም በግድ ዝጉ በማለት እያስፈራሩ በማዘጋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌም በምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ሮቢ ወረዳ በ16/10/07 በወረዳው አስተዳዳሪና በወረዳው ፖሊስ አዛዥ በተሰጠ ትዕዛዝ የኦፌኮ/መድረክ ቅ/ጽ/ቤት ተዘግቷል፡፡

ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትና በገዥው ፓርቲ የተፈጸሙት ተግባራት በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 54 ንዑስ አንቀጽ 1 #የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምፅ በምስጢር በሚሰጥበት ሥርዓት በየአምስት አመቱ በሕዝብ ይመረጣሉ&$ ተብሎ የተደነገገውን የጣሰ ነው፡፡ እንደዚሁም የየክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫን በሚመለከትም በየክልላዊ መንግሥታቱ ሕገመንግሥታት በተመሳሳይ የተደነገጉትን፣ በተሻሻለው የምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 አንቀፅ 26 በሰፈሩት የምርጫ መርሖዎችም #ማንኛውም ምርጫ ሁሉአቀፍ፣ ቀጥተኛ፣በምስጢር ድምፅ አሰጣጥ መራጩ ፈቃዱን በነፃነት የሚገለጽበት እና ያለምንም ልዩነት በእኩል ሕዝባዊ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ ይሆናል& የመምረጥ መመረጥ መብቱ በሕግ ያልተገደበ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብት አለው& እያንዳንዱ መራጭ የሚሰጠው ድምፅ እኩል ነው& ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ለመምረጥም ሆነ ለመመረጥ አይገደድም&$ ተብሎ የተደነገገውንም የጣሰ ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራችን የምርጫ ሥነምግባር ሕግ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 1 ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀምን አስመልክቶ #ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ፡- ያለውን የሥልጣን ኃላፊነትና የተለየ ዕድል ወይም ተፅዕኖ የማሳደር ችሎታ ለፖለቲካ ፍላጎቱ ለመጠቀም መደለያ ማቅረብን፣ ቅጣትንና ማንኛውንም የማስፈራሪያ መንገድ መጠቀምና የፈዴራል መንግሥትን፣ የክልል መንግሥታትን፣ የከተማ ማዘጋጃ ቤትን ወይም ሌላ የሕዝብ ሀብትን በምርጫ ሕጉ ከተፈቀደው አኳኋን ውጭ ለምርጫ ቅስቀሳ ዓላማ መጠቀም የለበትም&$የሚለውንም ድንጋጌ ያላከበረ ነው፡፡ የመንግሥት ሠራተኞችና ንብረት በሚመለከትም የመንግሥት ሠራተኛና ኃላፊ ሆኖ በራሱ የግል ጊዜ ካልሆነ በስተቀር በመንግሥት የሥራ ሰዓትና ኃላፊነት ተቋሙን በመጠቀም እጩዎችን ያስተዋወቀ ወይም ሌሎች እጩዎች ራሳቸውን በሕጋዊ መንገድ ለማስተዋወቅ ያላቸውን እድል ያደናቀፈ፣ በመንግሥት ንብረት ለምርጫ ቅስቀሳ የተጠቀመ፣ እንደሆነ የሥነምግባር ጥሰት እንደፈጸመ ይቆጠራል& ተብሎ በአንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 7 እና 8 የተደነገገውን በመጣስ የተፈጸሙ ሕገወጥ ተግባራት ናቸው፡፡

በአጠቃላይም በ2007 ዓ ም በሀገራችን ተካሄደ የተባለው ምርጫ በሕግና ሥርዓት ያልተመራና በሕገ-መንግሥቱና በምርጫ ሕጎች የተደነገጉትን የነፃ፣ፍትሐዊና ታአማኒነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መርሖዎች በኃይል በተጣሱበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ መድረክ የምርጫውን ሂደትም ሆነ ውጤት የማይቀበለው መሆኑን እየገለጸ፣ ለዚህ አሁን ሀገራችን ለገባችበት አስቸጋሪ ሁኔታ መፍትሔ ለማስገኘት የሚከተሉት እርምጃዎች እንዲወሰዱ በጥብቅ ይጠይቃል፡፡

1ኛ፡– በ2007 ዓ ም የተካሄደው 5ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ሂደትና ክንዋኔ በአጠቃላይ የሀገሪቱን ሕገመንግሥትና የምርጫ ሕጎች በጣሰ ሁኔታ የተከናወነ ስለሆነ፣ ይህንን ግዙፍ የሕግ ጥሰት አንድ ወገንተኛ ያልሆነ አካል ተቋቁሞ እንዲያጣራው፣

2ኛ፡- ከዚህ በላይ በተጠቀሱት አራት አባሎቻችን ላይ ግዲያ የፈጸሙ ወንጀለኞች ተገቢው ክትትል ተደርጎ ለሕግ እንዲቀርቡና ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው፣

3ኛ፡- ከምርጫው ቅስቀሳ ወቅት ጀምሮ በየምርጫ ክልሎቹ የታሰሩት አባሎቻችን ካለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱና የድብደባና የማሰቃየት ተግባራትን የፈጸሙባቸው የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣

4ኛ፡- ከምርጫው እንቅስቃሴ ወዲህ ቤታቸው የተቃጠለባቸው፣ የፈረሰባቸውና ንብረታቸው የተዘረፈባቸው አባሎቻችን ሀብትና ንብረት በአስቸኳይ እንዲመለስላቸውና እንዲከፈላቸው፣ በንብረታቸው ላይ ጉዳት ያደረሱ ካድሬዎችና የጸጥታ ኃይሎች አባላትም በሕግ እንዲጠየቁ፣

5ኛ፡- በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ካድሬዎች በማንአለብኝነት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየፈጸሙ የሚገኙት የማሸበር ተግባራት ማለትም በሰላማዊ ታጋዮቻችን ላይ በቀጣይነት እየተፈጸሙ ያሉት ግዲያዎች፣ ማስፈራራት፣ ወከባዎች፣ ዛቻዎችና የመሥራትና የመማር እንዲሁም እርዳታና አገልግሎት የማግኘት መብት በመንፈግ የሚፈጸሙ ሕገወጥ ተግባራት በአስቸኳይ እንዲቆሙ እንዲደረግና በዚህ አፍራሽና ፀረ ሰላም ተግባራቸው ምክንያት የሀገራችንና የሕዝባችን ሰላምና ደህንነት እንዳይናጋ ወቅታዊ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ፣

6ኛ፡- በ2007 ዓ ም በሀገራችን የተካሄደው ምርጫ ከሀገራችን ሕገ-መንግሥትና የምርጫ ሕጎች ውጭ መንግሥታዊ ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም ሕዝብን በማስፈራራት፣ በኃይልና በአፈና ገለልተኛ ታዛቢዎች በሌሉበት ገዥው ፓርቲ ራሱ ተወዳዳሪ፣ ዳኛና ታዛቢ ሆኖ ያካሄደውና በምንም መልኩ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ያልሆነና ታአማኒነት የሌለው ሕገወጥ ምርጫ ስለሆነ፣ገዥው ፓርቲ በገለልተኛ የምርጫ አስተዳዳር አማካይነት ገለልተኛ ታዛቢዎች በተገኙበት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ የሆነና ታአማኒነት ያለው ምርጫ ሊካሄድ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከመድረክና ሌሎች ሐቀኛ ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በአስቸኳይ በመደራደር ለነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክርሲያዊና ታዓማኒነት ላለው ምርጫ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠር እንዲደረግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

7ኛ፡- በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንዲረጋገጥ ሕጋዊ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ፣ እንደዚሁም ነፃ ፍትሐዊ ተዓማኒ ምርጫዎች ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይሳተፉ እንቅፋት የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ሁኔታዎችን ለማስወገድ ከኢህአዴግ ጋር የሚካሄድ ድርድርና የሌሎች ድርጅታዊ እንቅስቃሴዎች ውጤት በቀጣዩ ለመድረክ በምርጫዎች መሳተፍ ወሳኝ ይሆናል፡፡ ይህ የሰላማዊ መፍትሔ እርምጃ ከዚህ በፊት በኢህአዴግ አሻፈረኝ ባይነት ተቀባይነት አጥቶ ችግራችን እየተባባሰ እንዲሄድ ሲደረግ እንደቆየው ሁሉ አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጥሎ የሀገራችን ችግሮች እየተወሳሰቡና ከቁጥጥር ውጭ እየሆኑ ከሄዱ ኃላፊነቱ የኢህአዴግ ብቻ እንደሚሆን በቅድሚያ መግለጽ እንወዳለን፡፡

በመጨረሻም ነፃ፣ ፍትሐዊና ታአማኒ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለዘመናት ሲትናፍቅና ስትታገልለት የኖርከው ሰላም ወዳዱ መላው የሀገራችን ሕዝብ መድረክም ሆነ አባል ድርጅቶቹ በኢህአዴግ የ24 ዓመታት አገዛዝ በሀገራችን በተካሄዱት ምርጫዎች በመሳተፍና የሀገራችንን ችግሮች በሰላማዊ ውይይት ለመፍታትና የሕዝባችንን የሥልጣን ባለቤትነት በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማረጋገጥ ባካሄድናቸው ጥረቶች የኢህአዴግን በርካታ የግፍ ተግባራት በከፍተኛ ትዕግሥትና አርቆ አስተዋይነት ተቋቁመህ ከጎናችን በመሰለፍ ላበረከትከው አስተዋዖና ለከፈልከው መስዋዕትነት መድረክ ያለውን ታላቅ አክብሮትና ልባዊ ምስጋናውን ይገልጻል፡፡ የኢህአዴግ አገዛዝ ኃላፊነት በጎደለውና ሕግንና ሕገ-መንግሥትን በጣሰው እርምጃው የነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫን መንገድ ሙሉ በሙሉ በኃይል የዘጋብን ቢሆንም፣ በሀገራችን ሕገመንግሥት የተረጋገጡትና ገና ያልተጠቀምንባቸው የሰላማዊ የትግል ፈርጆች በርካታ ስለሆኑ በሰላማዊ የትግል አማራጫችን ጸንታችሁ አምባገነኑ የኢህአዴግ አገዘዝ ለሕግ የበላይነት እስኪገዛና ሰላማዊ የመፍትሔ ሐሳቦችን ተቀብሎ ሕገመንግሥታዊ መብቶች በተግባር እስኪረጋገጡ ድረስ ሰላማዊ ትግላችሁን ይበልጥ በተደራጃና በተጠናከረ መልኩ እንዲትቀጥሉ መድረክ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ድል ለሕዝባዊ ትግላችን!!

መድረክ
ሰኔ 19 ቀን 2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

Finfinnee, 26 May 2015

Related:

PRESS RELEASE: Amnesty International Asks Ethiopia to Investigate Suspicious Murders and Human Rights Violations

https://oromianeconomist.wordpress.com/2015/06/24/press-release-amnesty-international-asks-ethiopia-to-investigate-suspicious-murders-and-human-rights-violations/

Oromia: Ambo Defied TPLF’s Ban of Oromo’s Freedom of Assembly and Filled Stadium to Express Support for OFC for Upcoming Election April 23, 2015

Posted by OromianEconomist in Ambo, OFC, Oromia, Oromo, Oromo Federalist Congress.
Tags: , , , , , , , ,
add a comment

???????????Ambo Defied TPLF’s Ban of Oromo’s Freedom of Assembly and Filled Stadium to Express Support for OFCOromo Federalist Congress election campaign

Ambo Defied TPLF’s Ban of Oromo’s Freedom of Assembly and Filled Stadium to Express Support for OFC for Upcoming Election

 http://walabummaa43.blogspot.no/2015/04/ambo-defied-tplfs-ban-of-oromos-freedom.html
On April 20, 2015, Oromos in Ambo defied TPLF’s ban of Oromo’s freedom of assembly and filled a stadium, where Dr. Merera Gudina, Chairman of the Oromo Federalist Congress (OFC), was campaigning for the upcoming election (watch the video below). It’s to be noted that the TPLF regime tried to subdue Ambo a year ago during the Oromia-wide #OromoProtests against the ‘Addis Ababa Master Plan’ for Oromo Genocide. Almost a year ago, on April 30, 2014, more than 100 Oromo students and non-student civilians were killed by the Tigrean regime’s elite killing squad known as the Agazi Force; and thousands have been arrested just because they are Oromos, as an Amnesty International report revealed in October 2014. Shortly after April 2014, TPLF imposed on Oromia a sort of martial law where Oromos have been prohibited from assembly. On April 20, 2015, Ambo once again showed that it can never been subdued into submission by the TPLF state-sponsored terror by defying TPLF’s ban on Oromo’s freedom of assembly – and holding a rally to express support for OFC.
Meanwhile, another top OFC official, Obbo Baqqalaa Nagaa, is on campaign tour overseas to solicit support for his organization. According to the scheduleObbo Baqqalaa Nagaa will be meeting with supporters in Las Vegas on April 23, 2015, and in Seattle on April 25, 2015.
OFC/Medrek Election Campaign in Ambo with Dr. Merera Gudina:
OFC/Medrek Election Campaign in Gindeberet:
Read  more at: http://walabummaa43.blogspot.no/2015/04/ambo-defied-tplfs-ban-of-oromos-freedom.html
http://www.oromofederalistcongress.net/