In a joint statament OLF, OFC, ODF, UFIO & OLF-United say an attack on Oromo identity is taking place. የኦሮሞ ሕዝብ አንድነት እና አንገብጋቢ የወቅቱ ጉዳዮችን አስመልክቶ ኦነግ፣ ኦፌኮ፣ የተባበሩት ኦነግ፣ የኦሮሚያ ነፃነት አንድነት ግንባር እና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር የጋራ መግለጫ አውጥተዋል። September 25, 2018
Posted by OromianEconomist in Uncategorized.Tags: a joint statament OLF, Ethiopia, Finfinnee, ODF, ofc, Oromia, UFIO & OLF-United
trackback
Paartileen siyaasaa: ‘Gareen Oromoo balleessuuf gurmaa’ee socho’u akka jiru hubanneerra’

Paartileen siyaasaa Oromoo shan gochaan magaala Burraayyuufi Finfinnee keessatti Oromoota irratti raawwatame kan isaan gaddisiise ta’uu himan.
Dhaabbileen Oromoo shan KFO, ABO, ABO Tokkoome, Adda Dimokiraatawaa Oromoofi Addi Tokkummaa Walabummaa Oromoo haala siyaasaa biyyattii tibbanaa irratti erga Fulbaana 12 mariyatanii booda ibsa waliinii baasaniiru.
“Gareen Oromoo balleessuuf gurmaa’ee socho’u akka jiru hubanneerra” jedhan. Paartileen siyaasaa tokko tokkos namoonni dhaadanoowwan “Oromoofi Nootummaan Naannoo Oromiyaa magaala Finfinnee keessaa yaa bahan” jedhan qabatanii akka bahan godhaniiru.
Miidiyaalee rakkoo afarsan abaaruu
Dhaaboleen Oromoo shanan miidiyaalee ummataaf uummata walitti buusuuf hojjechaa jiran jedhanis balaalefataniiru.
“ESAT propogaandaafi olola maqaa balleessi Qeerroo irratti baneera” kan jedhan barreessaa Olaanaan KFO Obbo Baqqala Garbaa “miidiyichi Qeerroo bulguu fakkeessuun dhiyeessera” jedhaniiru.
Paartileen siyaasaa karaa nagaan dorgomuu hin barbaanne maallaqa sobaa namootaaf raabsuun okkara uumuufi mootummaan biyyattii bulchuu kan dadhabe fakkeessanii aangoo qabachuuf socho’aa akka jiranis Obbo Baqqalaan himaniiru.
Namoonni yakka raawwatan seeratti akka dhiyaataniif miseensonniifi deeggartoonni keenya mootummaa cinaa ni dhaabbatu jedhan.
“Namoota muraasaafi miidiyaa tokkoon biyyi yeroo diiggamu ilaaluu hin barbaadnu. Balaaleffachuu qofa osoo hin taanee namummaaf jennee uummata cinaa ni dhaabbanna.”
Ibsa waliin baasan kanaan halleellaa qabeenyaa akka manneen barnootaa Afaan Oromoo, baankiiwwaniifi kollejjootarra ga’es balaaleffataniiru.
Federaalizimii ilaalchisee
Sirna Federaalizimii rakkoo eenyummaa baroota dheeraaf Itoophiyaa keessa ture furuudhaaf diriirfame humnoonni dantaa hin qabne ka’umsi rakkoo kanaa federaalizimii akka ta’e mullisuudhaaf yaalii gochaa akka jiran ibsuudhaan ibsichi balaalleffateera.
Kanaaf, nuti paartileen Oromoo sochiin miidiyaalee dabalatee taasifamaa jiru kun balaa eenyummaa keenyarratti dhufe waan ta’eef cimsinee balaaleffanna, jedhaniiru.
የኦሮሞ ድርጅቶች፡ «ኦሮሞ እና አማራን የሚነጣጥሉ አይሳካላቸውም»

የኦሮሞ ሕዝብ አንድነት እና አንገብጋቢ የወቅቱ ጉዳዮችን አስመልክቶ ኦነግ፣ ኦፌኮ፣ የተባበሩት ኦነግ፣ የኦሮሚያ ነፃነት አንድነት ግንባር እና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
ፓርቲዎቹ በጋራ ባወጡት መግለጫ አምስት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ አተኩረዋል።
አነሱም የኦሮሞ ማንነትን ለማጥፋት እየተደረገ ያለው ሙከራ፣ አዲስ አበባ ጉዳይ፣ ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ ሚድያዎች፣ በሃገሪቱ እየታየ ያለው ለውጥን እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ፌዴራሊዝምን የሚመለከቱ ናቸው።
• የኦሮሞ ማንነት
ፓርቲዎቹ ሰሞኑን አደርግነው ባሉት ውይይት «ጠላቶቻችን የኦሮሞን ሕዝብ ለማጥፋት አሰቃቂ ግድያ ከመፈፀም አልፎ በኦሮሞ ሕዝብ ሰም የሚጠሩ ተቋማትን በማውደም ከፍተኛ ዝርፍያ ፈፅመዋል» ብለዋል።
«ከዚህ ጀርባ ፀረ ኦሮሞ አቋም ያለው የተደረጃ የፖለቲካ ቡድን ስለመኖሩ የሚያመለክቱ በርካታ መረጃዎች ተገኝተዋል» ይላል መግለጫው።
«በማንነታችን ላይ የተቃጣውን ድርጊት ከማንኛውም ጊዜ በላይ እናወግዛለን፤ ድርጊቱን የፈፀሙ በህግ እንዲጠየቁ እንጠይቃለን» በማለት ፓርቲዎቹ መግለጫቸው ላይ አትተዋል።
• አዲስ አበባን በተመለከተ
«ዛሬ አዲስ አበባ የምትገኝበት ሥፍራ የጥንት የኦሮሞ ጎሳዎች የእምነት፣ ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ማዕከል የነበረ መሆኑ አይካድም» የሚለው መግለጫው «ጎሳዎቹ መሬታቸውን ተነጥቀው እንዲጠፉ ተደርገዋል» ሲል ያክላል።
ፓርቲዎቹ «እኛ ኦሮሞ ድርጅቶች አዲስ አበባ ሁሌም የኦሮሞ ሕዝብ ናት፤ ይህ ማለት ግን ከኦሮሞ ውጭ መኖር አይችልም ማለት አይደለም» ሲሉ በመግለጫቸው አትተዋል።
«ሆኖም አንዳንድ የፖለቲካ ድርጀቶች ይህን በመካድ ከተማዋን እያሸበሩ መሆናቸውን ታዝበናል፤ አልፎም በኦሮሞ እና አማራ ሕዝብ መካል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ደፋ ቀና እያሉ ይገኛሉ። ቢሆንም አይሳካላቸውም፤ የኦሮሞ እና የአማራ ሕዝቦች ለውጥ ለማምጣት አብረው ታግለዋልና» ይላል መግለጫው።
መላው ሕዝብ የእኒህን ኃይሎች ሴራ ለማክሸፍ አብሮ መቆም አለበትም ሲል መግለጫው ያክላል።
• ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ ሚድያዎች
ለወገናዊ ፖለቲካ የሚያደሉ ሚድያዎች ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት ተግተው እየሰሩ እንደሆነ መግለጫው አትቷል።
«ስለዚህ ውጭም ሆነ ሃገር ቤት ያላችሁ ሃገር አማሽ ሚድያዎች በህግም በታሪክም ፊት ተጠያቂ መሆናችሁን አውቃችሁ ከድርጊታችሁ ታቀቡ» በማለት መግለጫው አስገንዝቧል።
• በሃገሪቷ እየታየ ያለውን ለውጥና ሽግግር በተመለከተ
«በሃገሪቱ ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታየ የመጣውን ለውጥና ፖለቲካዊ መነቃቃት ለውጡን በሚፈልጉ የሥርዓቱ አካላት የተገኘ እንደሆነ እናምናለን» የሚለው መግለጫው በዚህ የሽግግር ወቅት ስልጣን ላይ ያሉ አካላት ዘላቂ ለውጥ እንዲያመጡ ሁኔታዎችን እናመቻቻለን» የሚል አቋም ይዟል።
«ነገር ግን እንደማይሳካላቸው የተገነዘቡ የፖለቲካ ቡድኖች በሃሰት የብር ኖቶች ዜጎችን በማታለል የሃይማኖትና የብሄር ግጭት በማስነሳት መንግስት የሌለ ለማስመሰል እየተሯሯጡ እንደሆነ ግልጽ ነው።»
• ኦህዴድ አብዮታዊ ዴሞክራሲንና ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን ታሪክ ሊያደርጋቸው ይሆን?
«በመሆኑም አሁን ያሉ ተቋማት በህገ መንግሥቱ መሰረት በትክክል እንዲሰሩ ተደርጎ በነጻ፣ ተአማኒና በቂ ፉክክር በተደረገበት ህዝባዊ ምርጫ ወደ ዴሞክራሲ የሚደረገውን ሽግግር ብቻ የምንደግፍ መሆኑን እንገልጻለን» ሲሉ ድርጀቶቹ አቋማቸውን አንፀባርቀዋል።
• በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ፌደራሊዝምን በተመለከተ
ለዘመናት ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረውን የህዝቦች የማንነት ጥያቄ ለማክበር የተዘረጋውን የፌደራሊዝም ሥርዓት ደንታ የሌላቸው ኃይሎች ሥርዓቱ የችግሩ መንስኤ እንደሆነ አድርገው ለማቅረብ እየሞከሩ ነው ሲል መግለጫው ይወቅሳል።
አንዳንድ ሚዲያዎችም ይህንኑ ተግባር ተያይዘውታል። ስለዚህ እኛ የኦሮሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ፈጽሞ የማንቀበለው መሆኑንና በህልውናችን ላይ የተቃጣ አደጋ አድርገን እንደምንመለከተው እንገልጻለን በማለት ድርጀቶቹ መግለጫቸውን አጠናቀዋል።
Comments»